የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ኢሳይያስ 56
  • አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

ኢሳይያስ የመጽሐፉ ይዘት

      • የባዕድ አገር ሰውና ጃንደረባ የሚያገኙት በረከት (1-8)

        • ለሰው ሁሉ የሚሆን የጸሎት ቤት (7)

      • ዕውር ጠባቂዎች፤ መናገር የማይችሉ ውሾች (9-12)

ኢሳይያስ 56:1

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ሚክ 6:8
  • +ኢሳ 46:13፤ 51:5

ኢሳይያስ 56:2

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኢሳ 58:13, 14

ኢሳይያስ 56:3

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኢሳ 60:10፤ ዘካ 8:23

ኢሳይያስ 56:6

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ሚል 1:11

ኢሳይያስ 56:7

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኢሳ 2:3፤ ሚክ 4:2፤ ዘካ 8:3
  • +1ነገ 8:29, 43፤ ማቴ 21:13፤ ማር 11:17፤ ሉቃስ 19:46

ኢሳይያስ 56:8

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘዳ 30:3፤ ኢሳ 27:12፤ ሆሴዕ 1:11
  • +ኢሳ 49:22፤ 60:4

ኢሳይያስ 56:9

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኤር 12:9

ኢሳይያስ 56:10

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኢሳ 6:10፤ 29:10
  • +ኤር 6:13, 14፤ ሕዝ 13:16
  • +ሕዝ 33:6

ኢሳይያስ 56:11

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ብርቱ ነፍስ ያላቸው።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ሚክ 3:6

ኢሳይያስ 56:12

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኢሳ 5:22፤ 28:7፤ ሆሴዕ 4:11

ተዛማጅ ሐሳብ

ኢሳ. 56:1ሚክ 6:8
ኢሳ. 56:1ኢሳ 46:13፤ 51:5
ኢሳ. 56:2ኢሳ 58:13, 14
ኢሳ. 56:3ኢሳ 60:10፤ ዘካ 8:23
ኢሳ. 56:6ሚል 1:11
ኢሳ. 56:7ኢሳ 2:3፤ ሚክ 4:2፤ ዘካ 8:3
ኢሳ. 56:71ነገ 8:29, 43፤ ማቴ 21:13፤ ማር 11:17፤ ሉቃስ 19:46
ኢሳ. 56:8ዘዳ 30:3፤ ኢሳ 27:12፤ ሆሴዕ 1:11
ኢሳ. 56:8ኢሳ 49:22፤ 60:4
ኢሳ. 56:9ኤር 12:9
ኢሳ. 56:10ኢሳ 6:10፤ 29:10
ኢሳ. 56:10ኤር 6:13, 14፤ ሕዝ 13:16
ኢሳ. 56:10ሕዝ 33:6
ኢሳ. 56:11ሚክ 3:6
ኢሳ. 56:12ኢሳ 5:22፤ 28:7፤ ሆሴዕ 4:11
  • አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
  • 1
  • 2
  • 3
  • 4
  • 5
  • 6
  • 7
  • 8
  • 9
  • 10
  • 11
  • 12
አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
ኢሳይያስ 56:1-12

ኢሳይያስ

56 ይሖዋ እንዲህ ይላል፦

“ፍትሕን ጠብቁ፤+ ጽድቅ የሆነውንም አድርጉ፤

ማዳኔ በቅርቡ ይመጣልና፤

ጽድቄም ይገለጣል።+

 2 ይህን የሚያደርግ ሰው፣

ደግሞም ይህን አጥብቆ የሚይዝ፣

ሰንበትን የሚጠብቅና የማያረክስ፣+

እንዲሁም ከማንኛውም ዓይነት ክፋት እጁን የሚመልስ የሰው ልጅ ደስተኛ ነው።

 3 ከይሖዋ ጋር የሚቆራኝ የባዕድ አገር ሰው+

‘ይሖዋ ከሕዝቡ እንደሚለየኝ ጥርጥር የለውም’ አይበል።

ጃንደረባም ‘እነሆ፣ እኔ ደረቅ ዛፍ ነኝ’ አይበል።”

4 ይሖዋ እንዲህ ይላልና፦ “ሰንበቶቼን ለሚጠብቁ፣ ደስ የሚያሰኘኝን ነገር ለሚመርጡና ቃል ኪዳኔን አጥብቀው ለሚይዙ ጃንደረቦች፣

 5 በቤቴና በቅጥሮቼ ውስጥ

ከወንዶችና ከሴቶች ልጆች የሚሻል ነገር፣

ይኸውም የመታሰቢያ ሐውልትና ስም እሰጣቸዋለሁ።

ለዘላለም የማይጠፋ ስም እሰጣቸዋለሁ።

 6 እሱን ለማገልገል፣ የይሖዋን ስም ለመውደድና

የእሱ አገልጋዮች ለመሆን

ከይሖዋ ጋር የሚቆራኙትን የባዕድ አገር ሰዎች፣+

ሰንበትን የሚጠብቁትንና የማያረክሱትን፣

ቃል ኪዳኔንም አጥብቀው የሚይዙትን ሁሉ፣

 7 ቅዱስ ወደሆነው ተራራዬ አመጣቸዋለሁ፤+

በጸሎት ቤቴም ውስጥ እጅግ እንዲደሰቱ አደርጋቸዋለሁ።

የሚያቀርቧቸውም ሙሉ በሙሉ የሚቃጠሉ መባዎችና መሥዋዕቶች በመሠዊያዬ ላይ ተቀባይነት ያገኛሉ።

ቤቴም ለሕዝቦች ሁሉ የጸሎት ቤት ተብሎ ይጠራልና።”+

8 የተበተኑትን የእስራኤል ሰዎች የሚሰበስበው ሉዓላዊው ጌታ ይሖዋ+ እንዲህ ይላል፦

“አስቀድሞ ከተሰበሰቡት በተጨማሪ ሌሎችን ወደ እሱ እሰበስባለሁ።”+

 9 እናንተ በሜዳ ያላችሁ አራዊት ሁሉ፣

እናንተ በጫካ የምትኖሩ አራዊት ሁሉ፣ ኑና ብሉ።+

10 ጠባቂዎቹ ዕውሮች ናቸው፤+ አንዳቸውም አላስተዋሉም።+

ሁሉም መናገር የማይችሉ ውሾች ናቸው፤ መጮኽ አይችሉም።+

ተጋድመው ያለከልካሉ፤ እንቅልፍም ይወዳሉ።

11 በቀላሉ የማይጠግቡ* ውሾች ናቸው፤

ጠገብኩ ማለትን አያውቁም።

ማስተዋል የሌላቸው እረኞች ናቸው።+

ሁሉም በገዛ ራሳቸው መንገድ ሄደዋል፤

እያንዳንዳቸው አግባብ ያልሆነ ጥቅም ለማግኘት ይሻሉ፤ እንዲህም ይላሉ፦

12 “ኑ! የወይን ጠጅ ላምጣና

እስኪወጣልን ድረስ እንጠጣ።+

ነገም እንደ ዛሬ ይሆናል፤ እንዲያውም በጣም የተሻለ ይሆናል።”

የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ ጽሑፎች (2011-2025)
ውጣ
ግባ
  • የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ