5 በኢየሩሳሌም የተወለዱለት እነዚህ ናቸው፦+ ሺምአ፣ ሾባብ፣ ናታን+ እና ሰለሞን፤+ የእነዚህ የአራቱ ልጆች እናት የአሚዔል ልጅ ቤርሳቤህ+ ነበረች። 6 ሌሎቹ ዘጠኝ ወንዶች ልጆች ደግሞ ይብሃር፣ ኤሊሻማ፣ ኤሊፌሌት፣ 7 ኖጋ፣ ኔፌግ፣ ያፊአ፣ 8 ኤሊሻማ፣ ኤሊያዳ እና ኤሊፌሌት ናቸው። 9 ከቁባቶቹ ከወለዳቸው ወንዶች ልጆች ሌላ እነዚህ ሁሉ የዳዊት ወንዶች ልጆች ነበሩ፤ እህታቸውም ትዕማር+ ትባል ነበር።