የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • መዝሙር 22:16-18
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    • 16 ውሾች ከበውኛልና፤+

      እንደ ክፉ አድራጊዎች ሸንጎ በዙሪያዬ ሰፍረዋል፤+

      እንደ አንበሳ ሆነው እጆቼና እግሮቼ ላይ ተረባረቡ።*+

      17 አጥንቶቼን ሁሉ መቁጠር እችላለሁ።+

      እነሱም አዩኝ፤ ትኩር ብለውም ተመለከቱኝ።

      18 መደረቢያዎቼን እርስ በርሳቸው ተከፋፈሉ፤

      በልብሴም ላይ ዕጣ ተጣጣሉ።+

  • ኢሳይያስ 53:1-12
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    • 53 ከእኛ የሰማውን* ነገር ያመነ ማን ነው?+

      የይሖዋስ ክንድ+ ለማን ተገለጠ?+

       2 እሱ በፊቱ* እንደ ቅርንጫፍ፣+ በደረቅ ምድር እንዳለ ሥር ይበቅላል።

      የሚያምር ቁመናም ሆነ ግርማ ሞገስ የለውም፤+

      ባየነውም ጊዜ መልኩ አልሳበንም።*

       3 ሰዎች የናቁትና ያገለሉት፣+

      ሥቃይን ያየ፣* ሕመምንም የሚያውቅ ሰው ነበር።

      ፊቱ የተሰወረብን ያህል ነበር።*

      ሰዎች ናቁት፤ እኛም ከቁብ አልቆጠርነውም።+

       4 በእርግጥም እሱ ራሱ ሕመማችንን ተሸከመ፤+

      ሥቃያችንንም ተቀበለ።+

      እኛ ግን እንደተቀሰፈ፣ በአምላክ እንደተመታና እንደተጎሳቆለ አድርገን ቆጠርነው።

       5 እሱ ግን ስለ መተላለፋችን+ ተወጋ፤+

      ስለ በደላችን ደቀቀ።+

      በእሱ ላይ የደረሰው ቅጣት ለእኛ ሰላም አስገኘልን፤+

      በእሱም ቁስል የተነሳ እኛ ተፈወስን።+

       6 ሁላችንም እንደ በጎች ተቅበዘበዝን፤+

      እያንዳንዳችን በየራሳችን መንገድ ሄድን፤

      ይሖዋም የሁላችንንም በደል እሱ እንዲሸከም አደረገ።+

       7 ግፍ ተፈጸመበት፤+ መከራም ለመቀበል ፈቃደኛ ሆነ፤+

      ነገር ግን አፉን አልከፈተም።

      እንደ በግ ለመታረድ ተነዳ፤+

      በሸላቾቿ ፊት ዝም እንደምትል በግ፣

      እሱም አፉን አልከፈተም።+

       8 ፍትሕ ተነፈገ፤* በአግባቡም ሳይዳኝ ተወሰደ፤

      ትኩረት ሰጥቶ ትውልዱን በዝርዝር ለማወቅ* የሚሞክር ማን ነው?

      ከሕያዋን ምድር ተወግዷልና፤+

      በሕዝቤ መተላለፍ የተነሳ ተመታ።*+

       9 ምንም ዓይነት በደል* አልፈጸመም፤

      እንዲሁም ከአንደበቱ የማታለያ ቃል አልወጣም፤+

      ሆኖም በሚሞትበት ጊዜ የመቃብር ቦታው

      ከክፉዎችና+ ከሀብታሞች*+ ጋር ይሆናል።*

      10 ይሁንና እሱን ማድቀቅ የይሖዋ ፈቃድ ነበር፤* ለሕመም እንዲዳረግም ፈቅዷል።

      ሕይወቱን* የበደል መባ አድርገህ የምታቀርበው ከሆነ+

      ዘሩን ያያል፤ ዘመኑን ያስረዝማል፤+

      እንዲሁም በእሱ አማካኝነት ይሖዋ ደስ የሚሰኝበት ነገር* ይከናወናል።+

      11 በእሱ ላይ ከደረሰው ሥቃይ* የተነሳ፣ በሚያየው መልካም ነገር ይደሰታል።

      ጻድቅ አገልጋዬ+ በእውቀቱ አማካኝነት

      ብዙ ሰዎች ጻድቅ ሆነው እንዲቆጠሩ ይረዳል፤+

      በደላቸውንም ይሸከማል።+

      12 ስለዚህ ከብዙዎች ጋር ድርሻውን እሰጠዋለሁ፤

      ምርኮውን ከኃያላን ጋር ይካፈላል፤

      ሕይወቱን* እስከ ሞት ድረስ አፍስሷልና፤+

      ከሕግ ተላላፊዎችም ጋር ተቆጥሯል፤+

      የብዙ ሰዎችን ኃጢአት ተሸክሟል፤+

      ስለ ሕግ ተላላፊዎችም ማልዷል።+

  • ዳንኤል 9:26
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    • 26 “ከ62ቱ ሳምንታት በኋላ መሲሑ ይቆረጣል፤*+ ትቶት የሚያልፈው ምንም ነገር አይኖርም።+

      “የሚመጣውም መሪ ሠራዊት፣ ከተማዋንና ቅዱሱን ስፍራ ያጠፋል።+ ፍጻሜው በጎርፍ ይሆናል። እስከ ፍጻሜውም ድረስ ጦርነት ይሆናል፤ ጥፋትም ተወስኗል።+

የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ ጽሑፎች (2011-2025)
ውጣ
ግባ
  • የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ