የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ዘዳግም 12:5, 6
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    • 5 ከዚህ ይልቅ በነገዶቻችሁ ሁሉ መካከል ስሙን ሊያጸናበትና ማደሪያ ስፍራው ሊያደርገው በሚመርጠው በማንኛውም ቦታ አምላካችሁን ይሖዋን ፈልጉ፤ ወደዚያም ስፍራ ሂዱ።+ 6 የሚቃጠሉ መባዎቻችሁን፣+ መሥዋዕቶቻችሁን፣ አሥራቶቻችሁን፣+ ከእጃችሁ የሚዋጣውን መዋጮ፣+ የስእለት መባዎቻችሁን፣ የፈቃደኝነት መባዎቻችሁን+ እንዲሁም የከብታችሁንና የመንጋችሁን በኩራት+ የምትወስዱት ወደዚያ ስፍራ ነው።

  • 1 ነገሥት 9:3
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    • 3 ይሖዋም እንዲህ አለው፦ “በፊቴ የጸለይከውን ጸሎትና ሞገስ ለማግኘት ያቀረብከውን ልመና ሰምቻለሁ። የገነባኸውን ይህን ቤት ስሜ ለዘለቄታው እንዲጠራበት በማድረግ+ ቀድሼዋለሁ፤ ዓይኔም ሆነ ልቤ ሁልጊዜ በዚያ ይሆናል።+

  • 2 ዜና መዋዕል 7:12
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    • 12 ከዚያም ይሖዋ በሌሊት ለሰለሞን ተገልጦለት+ እንዲህ አለው፦ “ጸሎትህን ሰምቻለሁ፤ ይህን ቦታ መሥዋዕት የሚቀርብበት ቤት እንዲሆን ለራሴ መርጬዋለሁ።+

  • መዝሙር 122:በመዝሙሩ አናት ላይ የሚገኘው መግለጫ-9
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    • ወደ ላይ የመውጣት መዝሙር። የዳዊት መዝሙር።

      122 “ወደ ይሖዋ ቤት እንሂድ”

      ባሉኝ ጊዜ እጅግ ደስ አለኝ።+

       2 ኢየሩሳሌም ሆይ፣ አሁን በበሮችሽ ገብተን

      ከውስጥ ቆመናል።+

       3 ኢየሩሳሌም አንድ ወጥ ሆና

      እንደተገነባች ከተማ ናት።+

       4 ለእስራኤል በተሰጠው ማሳሰቢያ መሠረት፣

      ነገዶቹ ይኸውም የያህ* ነገዶች፣

      ለይሖዋ ስም ምስጋና ለማቅረብ

      ወደዚያ ወጥተዋል።+

       5 በዚያ የፍርድ ዙፋኖች፣

      የዳዊት ቤት ዙፋኖች+ ተቀምጠዋልና።+

       6 ለኢየሩሳሌም ሰላም ጸልዩ።+

      አንቺ ከተማ ሆይ፣ አንቺን የሚወዱ ከስጋት ነፃ ይሆናሉ።

       7 በመከላከያ ግንቦችሽ* ውስጥ ሰላም ለዘለቄታው ይኑር፤

      በማይደፈሩ ማማዎችሽ ውስጥ የተረጋጋ ሁኔታ ይስፈን።

       8 እንግዲህ ለወንድሞቼና ለወዳጆቼ ስል

      “በውስጥሽ ሰላም ይስፈን” እላለሁ።

       9 ለአምላካችን ለይሖዋ ቤት ስል+

      ለአንቺ መልካም ነገር እሻለሁ።

የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ ጽሑፎች (2011-2025)
ውጣ
ግባ
  • የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ