የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ ጽሑፎች (2011-2025)
ውጣ
ግባ
የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
ቤተ መጻሕፍታችንን በመጠቀምህ ደስ ብሎናል።
ይህ ቤተ መጻሕፍት የይሖዋ ምሥክሮች በተለያዩ ቋንቋዎች ያዘጋጇቸውን ጽሑፎች ተጠቅሞ ምርምር ለማድረግ ያስችላል።
የሕትመት ውጤቶችን ለማውረድ እባክህ jw.orgን ተጠቀም።
  • ዛሬ

ማክሰኞ፣ መስከረም 9

ማስተዋል የጎደላት ሴት ጯኺ ናት። እሷ ጨርሶ ማመዛዘን አትችልም።—ምሳሌ 9:13

“ማስተዋል የጎደላት ሴት” የምታቀርበውን ግብዣ የሚሰሙ ሰዎች ግብዣዋን ለመቀበል ወይም ላለመቀበል መወሰን ይኖርባቸዋል። ከፆታ ብልግና ለመራቅ የሚያነሳሱን አጥጋቢ ምክንያቶች አሉን። የምሳሌ መጽሐፍ፣ “ማስተዋል የጎደላት ሴት” “የተሰረቀ ውኃ ይጣፍጣል” እንደምትል ይናገራል። (ምሳሌ 9:17) “የተሰረቀ ውኃ” የሚለው አገላለጽ ምን ያመለክታል? መጽሐፍ ቅዱስ በትዳር አጋሮች መካከል የሚፈጸምን የፆታ ግንኙነት አርኪ ከሆነ ውኃ ጋር ያመሳስለዋል። (ምሳሌ 5:15-18) ሕጋዊ ጋብቻ የፈጸሙ ባለትዳሮች በፆታ ግንኙነት መደሰት ይችላሉ። ‘ከተሰረቀ ውኃ’ ጋር በተያያዘ ግን ሁኔታው በእጅጉ የተለየ ነው። ይህ አገላለጽ ያልተፈቀደ ወይም ከሥነ ምግባር ውጭ የሆነ የፆታ ግንኙነትን ሊያመለክት ይችላል። ሌቦች ብዙውን ጊዜ የሚሰርቁት ተደብቀው እንደሆነ ሁሉ ብዙዎች እንዲህ ያሉ ድርጊቶችን የሚፈጽሙት በድብቅ ነው። በተለይ ኃጢአት የሚፈጽሙት ሰዎች ድርጊታቸው ካልታወቀባቸው ደግሞ ‘የተሰረቀው ውኃ’ ይበልጥ ጣፋጭ መስሎ ሊታያቸው ይችላል። በዚህ መልኩ መታለላቸው እንዴት ያሳዝናል! ይሖዋ ሁሉንም ነገር ይመለከታል። የእሱን ሞገስ ማጣት ከምንም በላይ መራራ ነው፤ ስለዚህ የእሱን ሞገስ የሚያሳጣ ነገር ፈጽሞ ‘ጣፋጭ’ ሊሆን አይችልም።—1 ቆሮ. 6:9, 10፤ w23.06 22 አን. 7-9

ቅዱሳን መጻሕፍትን በየዕለቱ መመርመር—2025

ረቡዕ፣ መስከረም 10

ሳልወድ ባደርገውም እንኳ የመጋቢነት አደራ ተጥሎብኛል።—1 ቆሮ. 9:17

ጸሎትህ ተደጋጋሚ፣ አገልግሎትህ ደግሞ አሰልቺ እየሆነ እንደመጣ ቢሰማህስ? ‘የይሖዋን መንፈስ አጥቻለሁ’ የሚል መደምደሚያ ላይ ለመድረስ አትቸኩል። ፍጹም ስላልሆንክ ስሜትህ ሊለዋወጥ ይችላል። ቅንዓትህ መቀዝቀዝ ከጀመረ በሐዋርያው ጳውሎስ ምሳሌ ላይ አሰላስል። ጳውሎስ ኢየሱስን ለመምሰል ጥረት ቢያደርግም እንኳ አንዳንድ ጊዜ ተነሳሽነቱ ሊቀንስ እንደሚችል ተገንዝቧል። ጳውሎስ ስሜቱ ቢለዋወጥም እንኳ አገልግሎቱን ለማከናወን ቁርጥ ውሳኔ አድርጎ ነበር። አንተም ፍጹም ባልሆነው ስሜትህ ላይ ተመሥርተህ ውሳኔ ከማድረግ ተቆጠብ። ተነሳሽነት ባይኖርህም እንኳ ትክክለኛውን ነገር ለማድረግ ቁርጥ ውሳኔ አድርግ። ትክክለኛውን ነገር ማድረግህን ከቀጠልክ ውሎ አድሮ ተነሳሽነትህ ሊጨምር ይችላል።—1 ቆሮ. 9:16፤ w24.03 11-12 አን. 12-13

ቅዱሳን መጻሕፍትን በየዕለቱ መመርመር—2025

ሐሙስ፣ መስከረም 11

ለእነሱ ያላችሁን ፍቅር እውነተኝነት በተጨባጭ አስመሥክሩ።—2 ቆሮ. 8:24

ወንድሞቻችንና እህቶቻችን ጓደኞቻችን እንዲሆኑ በመፍቀድ ፍቅር ማሳየት እንችላለን። (2 ቆሮ. 6:11-13) በብዙዎቹ ጉባኤዎች ውስጥ የተለያየ አስተዳደግና ባሕርይ ያላቸው ወንድሞችና እህቶች ይገኛሉ። ባሏቸው መልካም ባሕርያት ላይ በማተኮር ለሁሉም ወንድሞቻችንና እህቶቻችን ያለንን ፍቅር ማሳደግ እንችላለን። ሌሎችን በይሖዋ ዓይን በማየት እንደምንወዳቸው እናስመሠክራለን። በታላቁ መከራ ወቅት ፍቅር በጣም አስፈላጊ ነገር ይሆናል። መከራው ሲጀምር ጥበቃ ማግኘት የምንችለው የት ነው? ይሖዋ በጥንቷ ባቢሎን ላይ ጥቃት ሲሰነዘር ለሕዝቡ ምን መመሪያ እንደሰጠ እንመልከት፦ “ሕዝቤ ሆይ፣ ሂድ ወደ ውስጠኛው ክፍልህ ግባ፤ በርህንም ከኋላህ ዝጋ። ቁጣው እስኪያልፍ ድረስ ለጥቂት ጊዜ ተሸሸግ።” (ኢሳ. 26:20) እነዚህ ቃላት ታላቁን መከራ ለምንጋፈጥ ክርስቲያኖችም የሚሠሩ ይመስላል። w23.07 6-7 አን. 14-16

ቅዱሳን መጻሕፍትን በየዕለቱ መመርመር—2025
ቤተ መጻሕፍታችንን በመጠቀምህ ደስ ብሎናል።
ይህ ቤተ መጻሕፍት የይሖዋ ምሥክሮች በተለያዩ ቋንቋዎች ያዘጋጇቸውን ጽሑፎች ተጠቅሞ ምርምር ለማድረግ ያስችላል።
የሕትመት ውጤቶችን ለማውረድ እባክህ jw.orgን ተጠቀም።
  • የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ