የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ ጽሑፎች (2011-2025)
ውጣ
ግባ
የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
ቤተ መጻሕፍታችንን በመጠቀምህ ደስ ብሎናል።
ይህ ቤተ መጻሕፍት የይሖዋ ምሥክሮች በተለያዩ ቋንቋዎች ያዘጋጇቸውን ጽሑፎች ተጠቅሞ ምርምር ለማድረግ ያስችላል።
የሕትመት ውጤቶችን ለማውረድ እባክህ jw.orgን ተጠቀም።
  • ዛሬ

ረቡዕ፣ መስከረም 10

ሳልወድ ባደርገውም እንኳ የመጋቢነት አደራ ተጥሎብኛል።—1 ቆሮ. 9:17

ጸሎትህ ተደጋጋሚ፣ አገልግሎትህ ደግሞ አሰልቺ እየሆነ እንደመጣ ቢሰማህስ? ‘የይሖዋን መንፈስ አጥቻለሁ’ የሚል መደምደሚያ ላይ ለመድረስ አትቸኩል። ፍጹም ስላልሆንክ ስሜትህ ሊለዋወጥ ይችላል። ቅንዓትህ መቀዝቀዝ ከጀመረ በሐዋርያው ጳውሎስ ምሳሌ ላይ አሰላስል። ጳውሎስ ኢየሱስን ለመምሰል ጥረት ቢያደርግም እንኳ አንዳንድ ጊዜ ተነሳሽነቱ ሊቀንስ እንደሚችል ተገንዝቧል። ጳውሎስ ስሜቱ ቢለዋወጥም እንኳ አገልግሎቱን ለማከናወን ቁርጥ ውሳኔ አድርጎ ነበር። አንተም ፍጹም ባልሆነው ስሜትህ ላይ ተመሥርተህ ውሳኔ ከማድረግ ተቆጠብ። ተነሳሽነት ባይኖርህም እንኳ ትክክለኛውን ነገር ለማድረግ ቁርጥ ውሳኔ አድርግ። ትክክለኛውን ነገር ማድረግህን ከቀጠልክ ውሎ አድሮ ተነሳሽነትህ ሊጨምር ይችላል።—1 ቆሮ. 9:16፤ w24.03 11-12 አን. 12-13

ቅዱሳን መጻሕፍትን በየዕለቱ መመርመር—2025

ሐሙስ፣ መስከረም 11

ለእነሱ ያላችሁን ፍቅር እውነተኝነት በተጨባጭ አስመሥክሩ።—2 ቆሮ. 8:24

ወንድሞቻችንና እህቶቻችን ጓደኞቻችን እንዲሆኑ በመፍቀድ ፍቅር ማሳየት እንችላለን። (2 ቆሮ. 6:11-13) በብዙዎቹ ጉባኤዎች ውስጥ የተለያየ አስተዳደግና ባሕርይ ያላቸው ወንድሞችና እህቶች ይገኛሉ። ባሏቸው መልካም ባሕርያት ላይ በማተኮር ለሁሉም ወንድሞቻችንና እህቶቻችን ያለንን ፍቅር ማሳደግ እንችላለን። ሌሎችን በይሖዋ ዓይን በማየት እንደምንወዳቸው እናስመሠክራለን። በታላቁ መከራ ወቅት ፍቅር በጣም አስፈላጊ ነገር ይሆናል። መከራው ሲጀምር ጥበቃ ማግኘት የምንችለው የት ነው? ይሖዋ በጥንቷ ባቢሎን ላይ ጥቃት ሲሰነዘር ለሕዝቡ ምን መመሪያ እንደሰጠ እንመልከት፦ “ሕዝቤ ሆይ፣ ሂድ ወደ ውስጠኛው ክፍልህ ግባ፤ በርህንም ከኋላህ ዝጋ። ቁጣው እስኪያልፍ ድረስ ለጥቂት ጊዜ ተሸሸግ።” (ኢሳ. 26:20) እነዚህ ቃላት ታላቁን መከራ ለምንጋፈጥ ክርስቲያኖችም የሚሠሩ ይመስላል። w23.07 6-7 አን. 14-16

ቅዱሳን መጻሕፍትን በየዕለቱ መመርመር—2025

ዓርብ፣ መስከረም 12

የዚህ ዓለም ትእይንት እየተለዋወጠ ነው።—1 ቆሮ. 7:31

ምክንያታዊ ነው የሚል ስም አትርፉ። ራሳችሁን እንዲህ እያላችሁ ጠይቁ፦ ‘ሰዎች ምክንያታዊ፣ እሺ ባይና ሰው የሚለኝን የምሰማ እንደሆንኩ ይሰማቸዋል? ወይስ ድርቅ ያልኩ፣ ግትርና አልሰማም ባይ አድርገው ይመለከቱኛል? ሌሎችን ለማዳመጥ፣ የሚቻል ከሆነም ሐሳባቸውን ለመቀበል ፈቃደኛ ነኝ?’ ይበልጥ ምክንያታዊ በሆንን መጠን ይሖዋንና ኢየሱስን ይበልጥ እንመስላለን። ምክንያታዊ መሆን፣ ለውጦች ሲያጋጥሙን ሁኔታዎችን እንደአመጣጣቸው ለማስተናገድ ያስችለናል። አንዳንድ ጊዜ ለውጦች ባልጠበቅነው አቅጣጫ ሕይወታችንን ሊያከብዱብን ይችላሉ። በድንገት ከባድ የጤና ችግር ሊያጋጥመን ይችላል፤ ወይም በምንኖርበት አካባቢ በኢኮኖሚው አሊያም በፖለቲካው ሥርዓት ላይ ድንገተኛ ለውጥ ተከስቶ ኑሯችን ሊመሰቃቀልብን ይችላል። (መክ. 9:11) የአገልግሎት ምድብ ለውጥ እንኳ ፈተና የሚሆንበት ጊዜ አለ። የሚከተሉትን አራት እርምጃዎች ከወሰድን አዲሱን ሁኔታ መልመድ ቀላል ይሆንልናል፦ (1) እውነታውን መቀበል፣ (2) ነገን አሻግሮ ማየት፣ (3) በጎ በጎውን ማሰብ እንዲሁም (4) ሌሎችን መርዳት። w23.07 21-22 አን. 7-8

ቅዱሳን መጻሕፍትን በየዕለቱ መመርመር—2025
ቤተ መጻሕፍታችንን በመጠቀምህ ደስ ብሎናል።
ይህ ቤተ መጻሕፍት የይሖዋ ምሥክሮች በተለያዩ ቋንቋዎች ያዘጋጇቸውን ጽሑፎች ተጠቅሞ ምርምር ለማድረግ ያስችላል።
የሕትመት ውጤቶችን ለማውረድ እባክህ jw.orgን ተጠቀም።
  • የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ