ዘካርያስ
10 “በበልግ ዝናብ ወቅት ይሖዋ ዝናብ እንዲያዘንብላችሁ ጠይቁ።
ከንቱ ስለሆኑ ሕልሞች ይናገራሉ፤
በከንቱም ሊያጽናኑ ይሞክራሉ።
ከዚህም የተነሳ ሕዝቡ እንደ በግ ይቅበዘበዛል።
እረኛ ስለሌለ ይሠቃያል።
3 በእረኞቹ ላይ ቁጣዬ ይነዳል፤
ጨቋኞቹንም መሪዎች* ተጠያቂ አደርጋቸዋለሁ፤
የሠራዊት ጌታ ይሖዋ ትኩረቱን ወደ መንጋው፣ ወደ ይሁዳ ቤት አዙሯልና፤+
ግርማ ሞገስ እንደተላበሰው የጦር ፈረሱ እነሱንም ግርማ ሞገስ አላብሷቸዋል።
5 እነሱም በጦርነት ጊዜ፣
በመንገድ ላይ ያለን ጭቃ እንደሚረግጡ ተዋጊዎች ይሆናሉ።
6 የይሁዳን ቤት ከሁሉ የላቀ አደርጋለሁ፤
የዮሴፍንም ቤት አድናለሁ።+
ምሕረት ስለማሳያቸው+
ቀድሞ ወደነበሩበት ሁኔታ እመልሳቸዋለሁ፤
እነሱም ፈጽሞ እንዳልጣልኳቸው ሰዎች ይሆናሉ፤+
እኔ ይሖዋ አምላካቸው ነኝና፤ ደግሞም እመልስላቸዋለሁ።
7 የኤፍሬም ሰዎች እንደ ኃያል ተዋጊ ይሆናሉ፤
ልባቸውም የወይን ጠጅ እንደጠጣ ሰው ሐሴት ያደርጋል።+
ልጆቻቸው ይህን አይተው ሐሴት ያደርጋሉ፤
ልባቸውም በይሖዋ ደስ ይለዋል።+
9 በሕዝቦች መካከል እንደ ዘር ብበትናቸውም፣
በሩቅ ስፍራዎች ሆነው ያስታውሱኛል፤
ከልጆቻቸው ጋር ሆነው ያንሰራራሉ፤ ደግሞም ይመለሳሉ።
የአሦር ኩራት ይዋረዳል፤
የግብፅም በትረ መንግሥት ይወገዳል።+