የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ዘካርያስ 10
  • አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

ዘካርያስ የመጽሐፉ ይዘት

      • ዝናብ ለማግኘት የሐሰት አማልክትን ሳይሆን ይሖዋን ጠይቁ (1, 2)

      • ይሖዋ ሕዝቡን አንድ ያደርጋል (3-12)

        • ከይሁዳ ቤት ቁልፍ የሆነ ሰው ይወጣል (3, 4)

ዘካርያስ 10:1

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘዳ 11:14፤ ኤር 14:22፤ 51:16፤ ሕዝ 34:26፤ ኢዩ 2:23

ዘካርያስ 10:2

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “የቤት ውስጥ አማልክት፤ ጣዖታት።”

  • *

    ወይም “ምትሃታዊ ነገር፤ አስማታዊ ነገር።”

ዘካርያስ 10:3

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ቃል በቃል “አውራ ፍየሎች።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ሕዝ 34:16, 17

ዘካርያስ 10:4

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ቃል በቃል “የማዕዘን ማማ።” ወሳኝ የሆነን ወይም ትልቅ ቦታ የሚሰጠውን ሰው ያመለክታል፤ አለቃ።

  • *

    ቃል በቃል “ማንጠልጠያና።” ድጋፍ የሚሰጥን ሰው ያመለክታል፤ ገዢ።

  • *

    ወይም “አሠሪዎች።”

ዘካርያስ 10:5

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘዳ 20:1
  • +ሐጌ 2:22

ዘካርያስ 10:6

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኤር 3:18፤ ሕዝ 37:16, 19፤ ሆሴዕ 1:10, 11
  • +ኤር 31:9, 20
  • +ኤር 30:18

ዘካርያስ 10:7

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘካ 9:15
  • +ኢሳ 66:14፤ ሶፎ 3:14

ዘካርያስ 10:8

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኢሳ 44:22፤ 51:11

ዘካርያስ 10:10

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኢሳ 11:11
  • +ኤር 50:19፤ ሚክ 7:14
  • +ኢሳ 49:19, 20፤ 54:1, 2

ዘካርያስ 10:11

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኢሳ 11:15
  • +ኢሳ 19:1፤ ሕዝ 30:13

ዘካርያስ 10:12

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኢሳ 41:10፤ 45:24
  • +ሚክ 4:5

ተዛማጅ ሐሳብ

ዘካ. 10:1ዘዳ 11:14፤ ኤር 14:22፤ 51:16፤ ሕዝ 34:26፤ ኢዩ 2:23
ዘካ. 10:3ሕዝ 34:16, 17
ዘካ. 10:5ዘዳ 20:1
ዘካ. 10:5ሐጌ 2:22
ዘካ. 10:6ኤር 3:18፤ ሕዝ 37:16, 19፤ ሆሴዕ 1:10, 11
ዘካ. 10:6ኤር 31:9, 20
ዘካ. 10:6ኤር 30:18
ዘካ. 10:7ዘካ 9:15
ዘካ. 10:7ኢሳ 66:14፤ ሶፎ 3:14
ዘካ. 10:8ኢሳ 44:22፤ 51:11
ዘካ. 10:10ኢሳ 11:11
ዘካ. 10:10ኤር 50:19፤ ሚክ 7:14
ዘካ. 10:10ኢሳ 49:19, 20፤ 54:1, 2
ዘካ. 10:11ኢሳ 11:15
ዘካ. 10:11ኢሳ 19:1፤ ሕዝ 30:13
ዘካ. 10:12ኢሳ 41:10፤ 45:24
ዘካ. 10:12ሚክ 4:5
  • አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
  • 1
  • 2
  • 3
  • 4
  • 5
  • 6
  • 7
  • 8
  • 9
  • 10
  • 11
  • 12
አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
ዘካርያስ 10:1-12

ዘካርያስ

10 “በበልግ ዝናብ ወቅት ይሖዋ ዝናብ እንዲያዘንብላችሁ ጠይቁ።

ነጎድጓድ የቀላቀለ ደመና የሚያመጣው፣

ለሰዎች ዝናብ የሚያዘንበው፣+

ለእያንዳንዱም በሜዳ ላይ የሚበቅለውን ተክል የሚሰጠው ይሖዋ ነው።

 2 የተራፊም ምስሎች* አታላይ ነገር* ተናግረዋልና፤

ሟርተኞችም የሐሰት ራእይ አይተዋል።

ከንቱ ስለሆኑ ሕልሞች ይናገራሉ፤

በከንቱም ሊያጽናኑ ይሞክራሉ።

ከዚህም የተነሳ ሕዝቡ እንደ በግ ይቅበዘበዛል።

እረኛ ስለሌለ ይሠቃያል።

 3 በእረኞቹ ላይ ቁጣዬ ይነዳል፤

ጨቋኞቹንም መሪዎች* ተጠያቂ አደርጋቸዋለሁ፤

የሠራዊት ጌታ ይሖዋ ትኩረቱን ወደ መንጋው፣ ወደ ይሁዳ ቤት አዙሯልና፤+

ግርማ ሞገስ እንደተላበሰው የጦር ፈረሱ እነሱንም ግርማ ሞገስ አላብሷቸዋል።

 4 ከእሱ ቁልፍ የሆነ ሰው፣*

ድጋፍ የሚሰጥ ገዢና*

የጦርነት ቀስት ይወጣል፤

ተቆጣጣሪዎች* ሁሉ፣ እያንዳንዳቸው ከእሱ ይወጣሉ።

 5 እነሱም በጦርነት ጊዜ፣

በመንገድ ላይ ያለን ጭቃ እንደሚረግጡ ተዋጊዎች ይሆናሉ።

ይሖዋ ከእነሱ ጋር ስለሆነ ይዋጋሉ፤+

የጠላት ፈረሰኞችም ኀፍረት ይከናነባሉ።+

 6 የይሁዳን ቤት ከሁሉ የላቀ አደርጋለሁ፤

የዮሴፍንም ቤት አድናለሁ።+

ምሕረት ስለማሳያቸው+

ቀድሞ ወደነበሩበት ሁኔታ እመልሳቸዋለሁ፤

እነሱም ፈጽሞ እንዳልጣልኳቸው ሰዎች ይሆናሉ፤+

እኔ ይሖዋ አምላካቸው ነኝና፤ ደግሞም እመልስላቸዋለሁ።

 7 የኤፍሬም ሰዎች እንደ ኃያል ተዋጊ ይሆናሉ፤

ልባቸውም የወይን ጠጅ እንደጠጣ ሰው ሐሴት ያደርጋል።+

ልጆቻቸው ይህን አይተው ሐሴት ያደርጋሉ፤

ልባቸውም በይሖዋ ደስ ይለዋል።+

 8 ‘አፏጭቼ አንድ ላይ እሰበስባቸዋለሁ፤

እዋጃቸዋለሁና፣+ ብዙ ይሆናሉ፤

መባዛታቸውንም ይቀጥላሉ።

 9 በሕዝቦች መካከል እንደ ዘር ብበትናቸውም፣

በሩቅ ስፍራዎች ሆነው ያስታውሱኛል፤

ከልጆቻቸው ጋር ሆነው ያንሰራራሉ፤ ደግሞም ይመለሳሉ።

10 ከግብፅ ምድር መልሼ አመጣቸዋለሁ፤

ከአሦርም አንድ ላይ እሰበስባቸዋለሁ፤+

ወደ ጊልያድ+ ምድርና ወደ ሊባኖስ አመጣቸዋለሁ፤

በቂ ስፍራም አይገኝላቸውም።+

11 እሱም ባሕሩን አስጨንቆ ያልፋል፤

በባሕሩም ውስጥ ሞገዱን ይመታል፤+

የአባይ ጥልቆች በሙሉ ይደርቃሉ።

የአሦር ኩራት ይዋረዳል፤

የግብፅም በትረ መንግሥት ይወገዳል።+

12 በይሖዋ ብርቱ አደርጋቸዋለሁ፤+

በስሙም ይሄዳሉ’+ ይላል ይሖዋ።”

የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ ጽሑፎች (2011-2025)
ውጣ
ግባ
  • የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ