-
1 ዜና መዋዕል 3:1-4አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
-
-
3 ዳዊት በኬብሮን ሳለ የተወለዱለት ወንዶች ልጆች እነዚህ ናቸው፦+ የበኩር ልጁ አምኖን፤+ እናቱ ኢይዝራኤላዊቷ አኪኖዓም+ ነበረች፤ ሁለተኛው ልጁ ዳንኤል፤ እናቱ ቀርሜሎሳዊቷ አቢጋኤል+ ነበረች፤ 2 የገሹር ንጉሥ የታልማይ ልጅ ከሆነችው ከማአካ የወለደው ሦስተኛው ልጁ አቢሴሎም፤+ ከሃጊት የወለደው አራተኛው ልጁ አዶንያስ፤+ 3 አምስተኛው ልጁ ሰፋጥያህ፤ እናቱ አቢጣል ነበረች፤ ስድስተኛው ልጁ ይትረአም፤ እናቱ የዳዊት ሚስት ኤግላ ነበረች። 4 እነዚህ ስድስቱ በኬብሮን ሳለ የተወለዱለት ናቸው፤ በዚያም ለ7 ዓመት ከ6 ወር ነገሠ፤ በኢየሩሳሌም ደግሞ 33 ዓመት ነገሠ።+
-