የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • 1 ነገሥት 9:8
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    • 8 ይህም ቤት የፍርስራሽ ክምር ይሆናል።+ በዚያም የሚያልፉ ሰዎች ሁሉ በመገረም ትኩር ብለው እየተመለከቱ ‘ይሖዋ በዚህች ምድርና በዚህ ቤት ላይ እንዲህ ያለ ነገር ያደረገው ለምንድን ነው?’+ በማለት ያፏጫሉ።

  • መዝሙር 74:3
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    •  3 ለዘለቄታው ወደፈራረሰው ቦታ አቅና።+

      ጠላት በቅዱሱ ስፍራ ያለውን ነገር ሁሉ አጥፍቷል።+

  • መዝሙር 79:1
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    • 79 አምላክ ሆይ፣ ብሔራት ርስትህን+ ወረውታል፤

      ቅዱስ መቅደስህንም አርክሰዋል፤+

      ኢየሩሳሌምን የፍርስራሽ ክምር አድርገዋታል።+

  • ኢሳይያስ 64:11
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    • 11 አባቶቻችን አንተን ያወደሱበት

      የቅድስናና የክብር ቤታችን*

      በእሳት ተቃጥሏል፤+

      ከፍ አድርገን እንመለከታቸው የነበሩት ነገሮች በሙሉ ፈራርሰዋል።

  • ኤርምያስ 7:14
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    • 14 ስለዚህ በሴሎ እንዳደረግኩት ሁሉ በስሜ በተጠራው፣+ እናንተም በምትታመኑበት በዚህ ቤት+ ላይ እንዲሁም ለእናንተና ለአባቶቻችሁ በሰጠሁት በዚህ ቦታ ላይ እንዲሁ አደርጋለሁ።+

  • ሰቆቃወ ኤርምያስ 1:10
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    • 10 ጠላት በውድ ሀብቶቿ ሁሉ ላይ እጁን አሳርፏል።+

      ወደ አንተ ጉባኤ እንዳይገቡ ያዘዝካቸው ብሔራት

      ወደ መቅደሷ ሲገቡ አይታለችና።+

  • ሰቆቃወ ኤርምያስ 2:7
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    •  7 ይሖዋ መሠዊያውን ናቀ፤

      መቅደሱን ተወ።+

      የማይደፈሩ ማማዎቿን ግንቦች ለጠላት አሳልፎ ሰጠ።+

      በበዓል ቀን እንደሚደረገው ሁሉ በይሖዋ ቤት በታላቅ ድምፅ ጮኹ።+

  • ሚክያስ 3:12
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    • 12 ስለዚህ በእናንተ የተነሳ

      ጽዮን እንደ እርሻ ትታረሳለች፤

      ኢየሩሳሌም የፍርስራሽ ክምር ትሆናለች፤+

      የቤቱም* ተራራ፣ በጫካ እንዳሉ ከፍ ያሉ ቦታዎች* ይሆናል።+

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ