-
አስቴር 9:5-10አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
-
-
5 አይሁዳውያኑ ጠላቶቻቸውን በሙሉ በሰይፍ ጨፈጨፏቸው፤ ገደሏቸው፤ እንዲሁም ደመሰሷቸው፤ በሚጠሏቸውም ሰዎች ላይ የፈለጉትን አደረጉባቸው።+ 6 አይሁዳውያኑ በሹሻን* ግንብ*+ 500 ሰዎችን ገደሉ፤ ደግሞም አጠፉ። 7 በተጨማሪም ፓርሻንዳታ፣ ዳልፎን፣ አስፋታ፣ 8 ፖራታ፣ አዳሊያ፣ አሪዳታ፣ 9 ፓርማሽታ፣ አሪሳይ፣ አሪዳይ እና ዋይዛታ የተባሉትን፣ 10 የአይሁዳውያን ጠላት+ የነበረውን የሃመዳታን ልጅ የሃማን አሥር ወንዶች ልጆች ገደሉ። ከገደሏቸው በኋላ ግን አንድም ምርኮ አልወሰዱም።+
-