ዘፀአት 17:6 አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ 6 እኔም በዚያ በኮሬብ በሚገኘው ዓለት ላይ ፊትህ እቆማለሁ። አንተም ዓለቱን ትመታዋለህ፤ ውኃም ከውስጡ ይፈልቃል፤ ሕዝቡም ይጠጣሉ።”+ ሙሴም የእስራኤል ሽማግሌዎች እያዩ እንደተባለው አደረገ። ዘኁልቁ 20:11 አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ 11 ሙሴም ይህን ካለ በኋላ እጁን አንስቶ ዓለቱን ሁለት ጊዜ በበትሩ መታው፤ ውኃውም ይንዶለዶል ጀመር፤ ማኅበረሰቡና ከብቶቻቸውም ጠጡ።+ መዝሙር 105:41 አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ 41 ዓለትን ሰነጠቀ፤ ውኃም ተንዶለዶለ፤+በበረሃ እንደ ወንዝ ፈሰሰ።+ ኢሳይያስ 48:21 አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ 21 ባድማ በሆኑ ቦታዎች በመራቸው ጊዜ አልተጠሙም።+ ከዓለት ውስጥ ውኃ አፈለቀላቸው፤ዓለቱን ሰንጥቆ ውኃ አንዶለዶለላቸው።”+ 1 ቆሮንቶስ 10:4 አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ 4 በተጨማሪም ሁሉም አንድ ዓይነት መንፈሳዊ መጠጥ ጠጡ።+ ይከተላቸው ከነበረው መንፈሳዊ ዓለት ይጠጡ ነበርና፤ ይህም ዓለት ክርስቶስን ያመለክታል።*+
6 እኔም በዚያ በኮሬብ በሚገኘው ዓለት ላይ ፊትህ እቆማለሁ። አንተም ዓለቱን ትመታዋለህ፤ ውኃም ከውስጡ ይፈልቃል፤ ሕዝቡም ይጠጣሉ።”+ ሙሴም የእስራኤል ሽማግሌዎች እያዩ እንደተባለው አደረገ።