መዝሙር 30:9 አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ 9 መሞቴና* ወደ ጉድጓድ* መውረዴ+ ምን የሚያስገኘው ጥቅም አለ? አፈር ያወድስሃል?+ የአንተንስ ታማኝነት ይናገራል?+ መዝሙር 115:17 አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ 17 ሙታንም ሆኑ ወደ ዝምታው ዓለም* የሚወርዱ ሁሉ፣+ያህን አያወድሱም።+ መክብብ 9:5 አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ 5 ሕያዋን እንደሚሞቱ ያውቃሉና፤+ ሙታን ግን ምንም አያውቁም፤+ ከእንግዲህም የሚያገኙት ብድራት* የለም፤ ምክንያቱም የሚታወሱበት ነገር ሁሉ ተረስቷል።+ መክብብ 9:10 አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ 10 እጅህ የሚያገኘውን ሥራ ሁሉ በሙሉ ኃይልህ አከናውን፤ አንተ በምትሄድበት በመቃብር* ሥራም ሆነ ዕቅድ፣ እውቀትም ሆነ ጥበብ የለምና።+