ምሳሌ 17:9 አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ 9 በደልን ይቅር የሚል* ሁሉ ፍቅርን ይሻል፤+አንድን ጉዳይ ደጋግሞ የሚያወራ ግን የልብ ጓደኛሞችን ይለያያል።+ 1 ቆሮንቶስ 13:4 አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ 4 ፍቅር+ ታጋሽና+ ደግ+ ነው። ፍቅር አይቀናም።+ ጉራ አይነዛም፣ አይታበይም፣+ 1 ቆሮንቶስ 13:7 አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ 7 ሁሉን ችሎ ያልፋል፣+ ሁሉን ያምናል፣+ ሁሉን ተስፋ ያደርጋል፣+ ሁሉን ነገር በጽናት ይቋቋማል።+ 1 ጴጥሮስ 4:8 አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ 8 ከሁሉም በላይ አንዳችሁ ለሌላው የጠለቀ ፍቅር ይኑራችሁ፤+ ምክንያቱም ፍቅር የኃጢአትን ብዛት ይሸፍናል።+