-
2 ነገሥት 19:22-24አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
-
-
22 ያቃለልከውና የሰደብከው ማንን ነው?+
ድምፅህን ከፍ ያደረግከው፣+
እብሪተኛ ዓይንህንም ያነሳኸው በማን ላይ ነው?
በእስራኤል ቅዱስ ላይ እኮ ነው!+
23 በመልእክተኞችህ+ በኩል ይሖዋን አቃለሃል፤+ እንዲህም ብለሃል፦
‘ብዛት ባላቸው የጦር ሠረገሎቼ፣
ወደ ተራሮች ከፍታ፣
ርቀው ወደሚገኙትም የሊባኖስ ስፍራዎች እወጣለሁ።
ረጃጅሞቹን አርዘ ሊባኖሶች፣ ምርጥ የሆኑትንም የጥድ ዛፎች እቆርጣለሁ።
ርቆ ወደሚገኘው ማረፊያ ቦታ፣ በጣም ጥቅጥቅ ወዳለው ጫካ እገባለሁ።
24 ጉድጓድ ቆፍሬ የባዕድ አገር ውኃዎችን እጠጣለሁ፤
የግብፅንም ጅረቶች* ሁሉ በእግሬ ረግጬ አደርቃለሁ።’
-