1 ቆሮንቶስ 9:27 አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ 27 ከዚህ ይልቅ ለሌሎች ከሰበክሁ በኋላ እኔ ራሴ በሆነ መንገድ ተቀባይነት እንዳላጣ* ሰውነቴን እየጎሰምኩ*+ እንደ ባሪያ እንዲገዛልኝ አደርገዋለሁ። ገላትያ 5:24 አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ 24 ከዚህም በተጨማሪ የክርስቶስ ኢየሱስ የሆኑት ሥጋን ከመጥፎ ምኞቱና ፍላጎቱ ጋር በእንጨት ላይ ቸንክረውታል።*+ ኤፌሶን 4:22 አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ 22 ከቀድሞ አኗኗራችሁ ጋር የሚስማማውንና አታላይ በሆነው ምኞቱ እየተበላሸ የሚሄደውን+ አሮጌውን ስብዕናችሁን* አውልቃችሁ እንድትጥሉ+ ተምራችኋል። ቆላስይስ 3:5 አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ 5 ስለዚህ በምድር ያሉትን የአካል ክፍሎቻችሁን ግደሉ፤+ እነሱም የፆታ ብልግና፣* ርኩሰት፣ ልቅ የሆነ የፍትወት ስሜት፣+ መጥፎ ፍላጎትና ጣዖት አምልኮ የሆነው ስግብግብነት ናቸው።
5 ስለዚህ በምድር ያሉትን የአካል ክፍሎቻችሁን ግደሉ፤+ እነሱም የፆታ ብልግና፣* ርኩሰት፣ ልቅ የሆነ የፍትወት ስሜት፣+ መጥፎ ፍላጎትና ጣዖት አምልኮ የሆነው ስግብግብነት ናቸው።