የሐዋርያት ሥራ 10:26 አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ 26 ጴጥሮስ ግን “ተነስ፣ እኔም እንደ አንተው ሰው ነኝ” ብሎ አስነሳው።+ የሐዋርያት ሥራ 10:28 አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ 28 እሱም እንዲህ አላቸው፦ “አንድ አይሁዳዊ ከሌላ ብሔር ከመጣ ሰው ጋር ይወዳጅ ወይም ይቀራረብ ዘንድ ሕጉ እንደማይፈቅድ በሚገባ ታውቃላችሁ፤+ ሆኖም አምላክ ማንንም ሰው ንጹሕ ያልሆነ ወይም ርኩስ ማለት እንደማይገባኝ ገልጦልኛል።+ የሐዋርያት ሥራ 11:2, 3 አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ 2 ስለዚህ ጴጥሮስ ወደ ኢየሩሳሌም በወጣ ጊዜ ግርዘትን የሚደግፉ ሰዎች+ ይተቹት* ጀመር፤ 3 “ወዳልተገረዙ ሰዎች ቤት ሄደህ ከእነሱ ጋር በልተሃል” አሉት።
28 እሱም እንዲህ አላቸው፦ “አንድ አይሁዳዊ ከሌላ ብሔር ከመጣ ሰው ጋር ይወዳጅ ወይም ይቀራረብ ዘንድ ሕጉ እንደማይፈቅድ በሚገባ ታውቃላችሁ፤+ ሆኖም አምላክ ማንንም ሰው ንጹሕ ያልሆነ ወይም ርኩስ ማለት እንደማይገባኝ ገልጦልኛል።+