ዕብራውያን 12:22 አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ 22 እናንተ ግን የቀረባችሁት ወደ ጽዮን ተራራና+ የሕያው አምላክ ከተማ ወደሆነችው ወደ ሰማያዊቱ ኢየሩሳሌም፣+ አንድ ላይ ወደተሰበሰቡ አእላፋት* መላእክት፣ ራእይ 3:12 አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ 12 “‘ድል የሚነሳውን በአምላኬ ቤተ መቅደስ ዓምድ አደርገዋለሁ፤ ከዚያ በኋላም በምንም ዓይነት ከዚያ አይወጣም፤ የአምላኬን ስምና+ ከሰማይ ከአምላኬ ዘንድ የምትወርደውን የአምላኬን ከተማ የአዲሲቱን ኢየሩሳሌም+ ስም እንዲሁም የእኔን አዲስ ስም በእሱ ላይ እጽፋለሁ።+ ራእይ 21:2 አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ 2 ደግሞም ቅድስቲቱ ከተማ፣ አዲሲቱ ኢየሩሳሌም ከሰማይ ከአምላክ ዘንድ ስትወርድ አየሁ፤+ እሷም ለባሏ እንዳጌጠች ሙሽራ ተዘጋጅታ ነበር።+
12 “‘ድል የሚነሳውን በአምላኬ ቤተ መቅደስ ዓምድ አደርገዋለሁ፤ ከዚያ በኋላም በምንም ዓይነት ከዚያ አይወጣም፤ የአምላኬን ስምና+ ከሰማይ ከአምላኬ ዘንድ የምትወርደውን የአምላኬን ከተማ የአዲሲቱን ኢየሩሳሌም+ ስም እንዲሁም የእኔን አዲስ ስም በእሱ ላይ እጽፋለሁ።+