የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ዘዳግም 17
  • አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

ዘዳግም የመጽሐፉ ይዘት

      • የሚቀርበው መሥዋዕት እንከን የለሽ መሆን አለበት (1)

      • ከሃዲዎችን በተመለከተ መደረግ ያለበት ነገር (2-7)

      • ለመዳኘት አስቸጋሪ የሆኑ የፍርድ ጉዳዮች (8-13)

      • ወደፊት ንጉሥ ቢያነግሡ መደረግ ያለበት ነገር (14-20)

        • ንጉሡ የሕጉን ቅጂ ለራሱ መገልበጥ ይኖርበታል (18)

ዘዳግም 17:1

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘሌ 22:20፤ ዘዳ 15:21፤ ሚል 1:8

ዘዳግም 17:2

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘዳ 4:23፤ 13:6-9

ዘዳግም 17:3

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘዳ 4:19
  • +ዘዳ 13:12-15

ዘዳግም 17:4

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዮሐ 7:51

ዘዳግም 17:5

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘዳ 13:6, 10

ዘዳግም 17:6

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ቃል በቃል “በሁለት ወይም በሦስት ሰዎች አፍ።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ማቴ 18:16፤ ዮሐ 8:17፤ 1ጢሞ 5:19፤ ዕብ 10:28
  • +ዘኁ 35:30፤ ዘዳ 19:15

ዘዳግም 17:7

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘዳ 13:5፤ 1ቆሮ 5:13

ማውጫዎች

  • የምርምር መርጃ

    የስብሰባው አስተዋጽኦ የማመሣከሪያ ጽሑፎች፣ 7/2021፣ ገጽ 5

    “ቅዱሳት መጻሕፍት ሁሉ” ጥራዝ 16፣ ገጽ 21

ዘዳግም 17:8

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘኁ 35:11
  • +ዘዳ 12:5፤ 1ነገ 3:16, 28፤ መዝ 122:2, 5

ዘዳግም 17:9

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ሳሙ 7:15, 16
  • +ዘዳ 19:17፤ 21:5

ዘዳግም 17:11

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ሚል 2:7
  • +ዘዳ 5:32፤ 12:32

ዘዳግም 17:12

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ምሳሌ 11:2፤ ዕብ 10:28
  • +ዘዳ 13:5፤ 1ቆሮ 5:13

ዘዳግም 17:13

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘዳ 13:11፤ 19:20

ዘዳግም 17:14

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ሳሙ 8:5, 20፤ 10:19

ዘዳግም 17:15

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ሳሙ 9:17፤ 10:24፤ 16:12, 13

ዘዳግም 17:16

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘዳ 20:1፤ 2ሳሙ 8:4፤ መዝ 20:7፤ ምሳሌ 21:31
  • +ኢሳ 31:1

ዘዳግም 17:17

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ነገ 11:1-3፤ ነህ 13:26
  • +ኢዮብ 31:24, 28፤ 1ጢሞ 6:9

ዘዳግም 17:18

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “በጥቅልል።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘዳ 31:9, 26፤ 2ነገ 22:8

ማውጫዎች

  • የምርምር መርጃ

    መጠበቂያ ግንብ፣

    3/15/2007፣ ገጽ 20

    5/1/1995፣ ገጽ 12-13

    “ቅዱሳት መጻሕፍት ሁሉ” ጥራዝ 7፣ ገጽ 3

ዘዳግም 17:19

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +መዝ 1:2፤ 119:97
  • +2ዜና 34:18

ማውጫዎች

  • የምርምር መርጃ

    መጠበቂያ ግንብ፣

    6/15/2002፣ ገጽ 12-17

    10/1/2000፣ ገጽ 8

    5/1/1995፣ ገጽ 12-13

ዘዳግም 17:20

ማውጫዎች

  • የምርምር መርጃ

    መጠበቂያ ግንብ፣

    5/1/1995፣ ገጽ 12-13

ተዛማጅ ሐሳብ

ዘዳ. 17:1ዘሌ 22:20፤ ዘዳ 15:21፤ ሚል 1:8
ዘዳ. 17:2ዘዳ 4:23፤ 13:6-9
ዘዳ. 17:3ዘዳ 4:19
ዘዳ. 17:3ዘዳ 13:12-15
ዘዳ. 17:4ዮሐ 7:51
ዘዳ. 17:5ዘዳ 13:6, 10
ዘዳ. 17:6ማቴ 18:16፤ ዮሐ 8:17፤ 1ጢሞ 5:19፤ ዕብ 10:28
ዘዳ. 17:6ዘኁ 35:30፤ ዘዳ 19:15
ዘዳ. 17:7ዘዳ 13:5፤ 1ቆሮ 5:13
ዘዳ. 17:8ዘኁ 35:11
ዘዳ. 17:8ዘዳ 12:5፤ 1ነገ 3:16, 28፤ መዝ 122:2, 5
ዘዳ. 17:91ሳሙ 7:15, 16
ዘዳ. 17:9ዘዳ 19:17፤ 21:5
ዘዳ. 17:11ሚል 2:7
ዘዳ. 17:11ዘዳ 5:32፤ 12:32
ዘዳ. 17:12ምሳሌ 11:2፤ ዕብ 10:28
ዘዳ. 17:12ዘዳ 13:5፤ 1ቆሮ 5:13
ዘዳ. 17:13ዘዳ 13:11፤ 19:20
ዘዳ. 17:141ሳሙ 8:5, 20፤ 10:19
ዘዳ. 17:151ሳሙ 9:17፤ 10:24፤ 16:12, 13
ዘዳ. 17:16ዘዳ 20:1፤ 2ሳሙ 8:4፤ መዝ 20:7፤ ምሳሌ 21:31
ዘዳ. 17:16ኢሳ 31:1
ዘዳ. 17:171ነገ 11:1-3፤ ነህ 13:26
ዘዳ. 17:17ኢዮብ 31:24, 28፤ 1ጢሞ 6:9
ዘዳ. 17:18ዘዳ 31:9, 26፤ 2ነገ 22:8
ዘዳ. 17:19መዝ 1:2፤ 119:97
ዘዳ. 17:192ዜና 34:18
  • አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
  • 1
  • 2
  • 3
  • 4
  • 5
  • 6
  • 7
  • 8
  • 9
  • 10
  • 11
  • 12
  • 13
  • 14
  • 15
  • 16
  • 17
  • 18
  • 19
  • 20
አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
ዘዳግም 17:1-20

ዘዳግም

17 “እንከን ወይም ማንኛውም ዓይነት ጉድለት ያለበትን በሬ ወይም በግ ለአምላክህ ለይሖዋ አትሠዋ፤ ምክንያቱም ይህ ለአምላክህ ለይሖዋ አስጸያፊ ነው።+

2 “አምላክህ ይሖዋ ከሚሰጥህ ከተሞች በአንዱ ውስጥ በአምላክህ በይሖዋ ፊት መጥፎ የሆነውን ነገር የሚፈጽምና ቃል ኪዳኑን የሚያፈርስ ወንድ ወይም ሴት ቢገኝ+ 3 እሱም ሄዶ ሌሎች አማልክትን በማምለክ እንዲሁም ለእነሱ ወይም ለፀሐይ አሊያም ለጨረቃ ወይም ደግሞ ለሰማይ ሠራዊት በሙሉ በመስገድ+ እኔ ያላዘዝኩትን ነገር ቢያደርግ+ 4 አንተም ይህ ነገር ቢነገርህ ወይም ሁኔታውን ብትሰማ ጉዳዩን በጥንቃቄ አጣራ። ይህ አስጸያፊ ነገር በእስራኤል ውስጥ መፈጸሙ እውነት እንደሆነ ቢረጋገጥ+ 5 እንዲህ ያለ መጥፎ ድርጊት የፈጸመውን ያንን ሰው ወይም ያቺን ሴት ወደ ከተማዋ በር አውጣቸው፤ ከዚያም ሰውየው ወይም ሴትየዋ እስኪሞቱ ድረስ በድንጋይ ይወገሩ።+ 6 ሞት የሚገባው ሰው ሁለት ወይም ሦስት ሰዎች በሚሰጡት ምሥክርነት*+ ይገደል። አንድ ምሥክር በሚሰጠው ቃል ብቻ መገደል የለበትም።+ 7 እሱን ለመግደል መጀመሪያ እጃቸውን የሚያነሱት ምሥክሮቹ መሆን ይኖርባቸዋል፤ ከዚያም ሕዝቡ ሁሉ እጁን ያንሳበት። ክፉ የሆነውን ከመካከልህ አስወግድ።+

8 “ከከተሞችህ በአንዱ ውስጥ ለመዳኘት አስቸጋሪ የሆነ ክርክር ቢነሳ ለምሳሌ፣ ጉዳዩ ደም ማፍሰስን+ የሚመለከትም ይሁን ለሕግ አቤቱታ ማቅረብን ወይም የዓመፅ ድርጊትን አሊያም ሌሎች አለመግባባቶችን የሚመለከት ቢሆን ተነስተህ አምላክህ ይሖዋ ወደሚመርጠው ስፍራ ውጣ።+ 9 ወደ ሌዋውያን ካህናትና በዚያን ጊዜ ዳኛ ሆኖ ወደሚያገለግለው ሰው+ ሄደህ ጠይቅ፤ እነሱም ውሳኔውን ይነግሩሃል።+ 10 አንተም እነዚህ ሰዎች ይሖዋ በሚመርጠው ስፍራ ሆነው በነገሩህ ውሳኔ መሠረት እርምጃ ውሰድ። የሰጡህንም መመሪያ በሙሉ በጥንቃቄ ፈጽም። 11 በሚሰጡህ ሕግና በሚነግሩህ ውሳኔ መሠረት እርምጃ ውሰድ።+ እነሱ ካሳለፉት ውሳኔ ወደ ቀኝም ሆነ ወደ ግራ ዞር አትበል።+ 12 አምላክህን ይሖዋን የሚያገለግለውን ካህን ወይም ዳኛውን ባለመስማት እብሪተኛ የሚሆን ሰው ካለ ይገደል።+ ክፉ የሆነውን ከእስራኤል መካከል አስወግድ።+ 13 ሕዝቡም ሁሉ ይህን ሲሰማ ይፈራል፤ ከእንግዲህም የእብሪት ድርጊት አይፈጽምም።+

14 “አምላክህ ይሖዋ የሚሰጥህን ምድር ገብተህ ከወረስካት በኋላ በዚያ መኖር ስትጀምር ‘በዙሪያዬ እንዳሉት ብሔራት ሁሉ እኔም በላዬ ላይ ንጉሥ ላንግሥ’ ብትል+ 15 አምላክህ ይሖዋ የሚመርጠውን ንጉሥ ታነግሣለህ። የምታነግሠውም ንጉሥ ከወንድሞችህ መካከል መሆን ይኖርበታል።+ ወንድምህ ያልሆነን ባዕድ ሰው በላይህ ላይ ማንገሥ አይገባህም። 16 ይሁን እንጂ ንጉሡ ለራሱ ፈረሶች ማብዛት+ ወይም የፈረሶቹን ቁጥር ለመጨመር ሲል ሕዝቡ ወደ ግብፅ እንዲመለስ ማድረግ የለበትም፤+ ምክንያቱም ይሖዋ ‘በዚህ መንገድ ፈጽሞ ዳግመኛ እንዳትመለሱ’ ብሏችኋል። 17 ልቡ ከትክክለኛው መንገድ ዞር እንዳይል ለራሱ ሚስቶች አያብዛ፤+ ለራሱም ብርና ወርቅ አያከማች።+ 18 በመንግሥቱ ዙፋን ላይ በሚቀመጥበትም ጊዜ በሌዋውያን ካህናት እጅ ካለው ላይ ወስዶ የዚህን ሕግ ቅጂ ለራሱ በመጽሐፍ* ላይ ይጻፍ።+

19 “አምላኩን ይሖዋን መፍራትን እንዲማር እንዲሁም በዚህ ሕግና በእነዚህ ሥርዓቶች ላይ የሰፈሩትን ቃላት በሙሉ በመፈጸም እንዲጠብቃቸው ይህ መጽሐፍ ከእሱ ጋር ይሁን፤+ በሕይወት ዘመኑም ሁሉ ያንብበው።+ 20 ይህን ካደረገ ልቡ በወንድሞቹ ላይ አይታበይም፤ ከትእዛዛቱም ወደ ቀኝም ሆነ ወደ ግራ ዞር አይልም፤ ይህም እሱም ሆነ ልጆቹ በእስራኤል መካከል በመንግሥቱ ላይ ረጅም ዘመን እንዲቆዩ ያስችላቸዋል።

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ