የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • መዝሙር 60
  • አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

መዝሙር የመጽሐፉ ይዘት

      • አምላክ ጠላቶችን አሸነፈ

        • “የሰው ማዳን ከንቱ ነው” (11)

        • “አምላክ ኃይል ይሰጠናል” (12)

መዝሙር 60:በመዝሙሩ አናት ላይ የሚገኘው መግለጫ

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    የቃላት መፍቻውን ተመልከት።

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +2ሳሙ 8:13፤ 1ዜና 18:3

መዝሙር 60:1

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +መዝ 60:10

መዝሙር 60:3

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኢሳ 51:17

መዝሙር 60:4

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    “አቆምክላቸው” ማለትም ሊሆን ይችላል።

መዝሙር 60:5

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +መዝ 18:35፤ 21:8፤ 108:6፤ 118:15፤ ኢሳ 41:10

መዝሙር 60:6

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    “በቅዱስ ስፍራው” ማለትም ሊሆን ይችላል።

  • *

    ወይም “ረባዳማ ሜዳ።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 12:6, 7
  • +ኢያሱ 13:27, 28፤ መዝ 108:7-9

መዝሙር 60:7

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ቃል በቃል “ለራሴ ምሽግ ነው።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኢያሱ 13:29-31
  • +ዘፍ 49:10

መዝሙር 60:8

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘኁ 24:17፤ 2ሳሙ 8:2
  • +ዘኁ 24:18፤ 2ሳሙ 8:14
  • +2ሳሙ 8:1

መዝሙር 60:9

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    “ወደተመሸገችው” ማለትም ሊሆን ይችላል።

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +2ሳሙ 8:14፤ መዝ 108:10-13

መዝሙር 60:10

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘዳ 1:42፤ 20:4፤ ኢያሱ 7:12

መዝሙር 60:11

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +መዝ 62:9፤ 118:8፤ 146:3

መዝሙር 60:12

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +መዝ 18:32
  • +2ሳሙ 10:12፤ መዝ 44:5

ተዛማጅ ሐሳብ

መዝ. 60:በመዝሙሩ አናት ላይ የሚገኘው መግለጫ2ሳሙ 8:13፤ 1ዜና 18:3
መዝ. 60:1መዝ 60:10
መዝ. 60:3ኢሳ 51:17
መዝ. 60:5መዝ 18:35፤ 21:8፤ 108:6፤ 118:15፤ ኢሳ 41:10
መዝ. 60:6ዘፍ 12:6, 7
መዝ. 60:6ኢያሱ 13:27, 28፤ መዝ 108:7-9
መዝ. 60:7ኢያሱ 13:29-31
መዝ. 60:7ዘፍ 49:10
መዝ. 60:8ዘኁ 24:17፤ 2ሳሙ 8:2
መዝ. 60:8ዘኁ 24:18፤ 2ሳሙ 8:14
መዝ. 60:82ሳሙ 8:1
መዝ. 60:92ሳሙ 8:14፤ መዝ 108:10-13
መዝ. 60:10ዘዳ 1:42፤ 20:4፤ ኢያሱ 7:12
መዝ. 60:11መዝ 62:9፤ 118:8፤ 146:3
መዝ. 60:12መዝ 18:32
መዝ. 60:122ሳሙ 10:12፤ መዝ 44:5
  • አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
  • 1
  • 2
  • 3
  • 4
  • 5
  • 6
  • 7
  • 8
  • 9
  • 10
  • 11
  • 12
አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
መዝሙር 60:1-12

መዝሙር

ለሙዚቀኞች ቡድን መሪ፤ “በማስታወሻ አበባ” የሚዘመር። ሚክታም።* የዳዊት መዝሙር። ለትምህርት። ከአራምናሃራይም እና ከአራምጾባ ሰዎች ጋር በተዋጋ ጊዜ፤ ኢዮዓብም ተመልሶ በጨው ሸለቆ 12,000 ኤዶማውያንን ፈጀ።+

60 አምላክ ሆይ፣ ገሸሽ አድርገኸናል፤ መከላከያዎቻችንን ጥሰህ አልፈሃል።+

ተቆጥተኸናል፤ አሁን ግን መልሰህ ተቀበለን!

 2 ምድርን አናወጥካት፤ ሰነጣጠቅካት።

እየፈራረሰች ነውና ስንጥቆቿን ጠግን።

 3 ሕዝብህ መከራ እንዲደርስበት አደረግክ።

የወይን ጠጅ እንድንጠጣና እንድንንገዳገድ አደረግከን።+

 4 አንተን የሚፈሩ ከቀስት መሸሽና ማምለጥ እንዲችሉ

ምልክት አቁምላቸው።* (ሴላ)

 5 የምትወዳቸው ሰዎች እንዲድኑ

በቀኝ እጅህ ታደገን፤ ደግሞም መልስ ስጠን።+

 6 አምላክ በቅድስናው* እንዲህ ብሏል፦

“ሐሴት አደርጋለሁ፤ ሴኬምን ርስት አድርጌ እሰጣለሁ፤+

የሱኮትንም ሸለቆ* አከፋፍላለሁ።+

 7 ጊልያድም ሆነ ምናሴ የእኔ ናቸው፤+

ኤፍሬምም የራስ ቁሬ ነው፤*

ይሁዳ በትረ መንግሥቴ ነው።+

 8 ሞዓብ መታጠቢያ ገንዳዬ ነው።+

በኤዶም ላይ ጫማዬን እጥላለሁ።+

በፍልስጤም ላይ በድል አድራጊነት እጮኻለሁ።”+

 9 ወደተከበበችው* ከተማ ማን ይወስደኛል?

እስከ ኤዶም ድረስ ማን ይመራኛል?+

10 አምላክ ሆይ፣ ገሸሽ ያደረግከን አንተ አይደለህም?

አምላካችን ሆይ፣ ከሠራዊታችን ጋር አብረህ አትወጣም።+

11 ከጭንቅ እንድንገላገል እርዳን፤

የሰው ማዳን ከንቱ ነውና።+

12 አምላክ ኃይል ይሰጠናል፤+

ጠላቶቻችንንም ይረጋግጣቸዋል።+

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ