የርዕስ ማውጫ
ጥር 15, 2013
© 2013 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania. የባለቤቱ መብት በሕግ የተጠበቀ ነው።
የጥናት እትም
የካቲት 25, 2013-መጋቢት 3, 2013
ገጽ 7 • መዝሙሮች፦ 49, 23
መጋቢት 4-10, 2013
ገጽ 12 • መዝሙሮች፦ 27, 51
መጋቢት 11-17, 2013
ገጽ 17 • መዝሙሮች፦ 52, 32
መጋቢት 18-24, 2013
ገጽ 22 • መዝሙሮች፦ 51, 39
መጋቢት 25-31, 2013
‘ለደስታችን ከእኛ ጋር አብረው የሚሠሩት’ ክርስቲያን ሽማግሌዎች
ገጽ 27 • መዝሙሮች፦ 42, 53
የጥናት ርዕሶች
▪ ደፋር ሁኑ—ይሖዋ ከእናንተ ጋር ነው!
እምነትና ድፍረት ያሳዩ በርካታ የአምላክ አገልጋዮች በቅዱሳን መጻሕፍት ውስጥ ተጠቅሰዋል። የእነሱን ተሞክሮ መመርመር እምነታችንን የሚያጠናክርልን ከመሆኑም ሌላ አምላክን በድፍረት ለማገልገል ያነሳሳናል። ይህ ርዕስ የ2013ን የዓመት ጥቅስ የሚያብራራ ነው።
▪ ምንም ነገር ከይሖዋ እንዲያርቃችሁ አትፍቀዱ
▪ ምንጊዜም ወደ ይሖዋ ቅረቡ
ወላጆቻችንን፣ ወንድሞቻችንንና እህቶቻችንን እንዲሁም የትውልድ ቦታችንን ጨምሮ በሕይወታችን ውስጥ በእኛ ምርጫ የማይከናወኑ ብዙ ነገሮች አሉ። ከይሖዋ ጋር ያለንን ዝምድና በተመለከተ ግን ሁኔታው የተለየ ነው። ወደ አምላክ ለመቅረብ አሊያም ከእሱ ለመራቅ መምረጥ እንችላለን። በእነዚህ ርዕሶች ላይ በሕይወታችን ውስጥ ከሚያጋጥሙን ከይሖዋ ሊያርቁን ከሚችሉ ነገሮች መካከል ሰባቱን እንመረምራለን።
▪ ከጸጸት ስሜት ነፃ ሆኖ ማገልገል
ሁላችንም ብንሆን ወደ ኋላ መመለስ ቢቻል ኖሮ በተለየ መንገድ እናደርጋቸው እንደነበረ የሚሰሙን ነገሮች አይጠፉም። ያም ቢሆን እንዲህ ያለው የጸጸት ስሜት በይሖዋ አገልግሎት ከመካፈል እንዲያግደን ልንፈቅድለት አይገባም። ከጸጸት ስሜት ነፃ ሆኖ በማገልገል ረገድ ከሐዋርያው ጳውሎስ ምን ትምህርት እንደምናገኝ በዚህ ርዕስ ላይ እንመለከታለን።
▪ ‘ለደስታችን ከእኛ ጋር አብረው የሚሠሩት’ ክርስቲያን ሽማግሌዎች
ጳውሎስ ለቆሮንቶስ ክርስቲያኖች በጻፈው ሁለተኛ ደብዳቤው ላይ እሱና የሥራ አጋሮቹ ‘ለደስታቸው ከእነሱ ጋር አብረው እንደሚሠሩ’ ገልጾላቸዋል። (2 ቆሮ. 1:24) እነዚህ ቃላት በተለይ በዛሬው ጊዜ ለሚገኙ ክርስቲያን ሽማግሌዎች ምን ትርጉም አላቸው? እያንዳንዳችን የጉባኤው ደስታ እንዲጨምር የበኩላችንን አስተዋጽኦ ማበርከት የምንችለውስ እንዴት ነው? የእነዚህ ጥያቄዎች መልስ በዚህ ርዕስ ውስጥ ይብራራል።
በተጨማሪም በዚህ እትም ውስጥ
ሽፋኑ፦ ጡረታ የወጡ ባልና ሚስት በካምፕ ፔሪን በሚገኝ አንድ ቤት ውስጥ በረንዳ ላይ ሆነው የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ሲመሩ። እንደነዚህ ባልና ሚስት ሁሉ ባሕር ማዶ የሚኖሩ አንዳንድ የሄይቲ ዜጎች፣ የመንግሥቱ ሰባኪዎች ይበልጥ በሚያስፈልጉባቸው አካባቢዎች ለማገልገል ሲሉ ወደ ትውልድ አገራቸው እየተመለሱ ነው
ሄይቲ
ለአንድ አስፋፊ ምን ያህል ሰው እንደሚደርስ የሚያሳይ ሬሾ
1:557
አስፋፊዎች
17,954
የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናቶች
35,735