የርዕስ ማውጫ
ጥር 15, 2014
© 2014 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania.
የጥናት እትም
መጋቢት 3-9, 2014
ገጽ 7 • መዝሙሮች፦ 27, 46
መጋቢት 10-16, 2014
ለ100 ዓመት የዘለቀ ንጉሣዊ አገዛዝ —የአንተን ሕይወት የሚነካው እንዴት ነው?
ገጽ 12 • መዝሙሮች፦ 17, 10
መጋቢት 17-23, 2014
ገጽ 17 • መዝሙሮች፦ 41, 11
መጋቢት 24-30, 2014
ገጽ 22 • መዝሙሮች፦ 54, 17
መጋቢት 31, 2014–ሚያዝያ 6, 2014
ገጽ 27 • መዝሙሮች፦ 14, 30
የጥናት ርዕሶች
▪ የዘላለሙን ንጉሥ ይሖዋን አምልኩ
ይህ ርዕስ ይሖዋ ምንጊዜም ንጉሥ መሆኑን የሚያረጋግጥልን ከመሆኑም ሌላ በሰማይና በምድር የሚገኙትን ፍጥረታቱን የገዛው እንዴት እንደሆነ ይገልጻል። የዘላለም ንጉሥ የሆነውን ይሖዋን ለማምለክ የመረጡትን በጥንት ጊዜ የነበሩትን አገልጋዮቹን ምሳሌ እንድንከተልም ያበረታታናል።
▪ ለ100 ዓመት የዘለቀ ንጉሣዊ አገዛዝ—የአንተን ሕይወት የሚነካው እንዴት ነው?
ይህ ርዕስ መሲሐዊው መንግሥት ባለፉት 100 ዓመታት ውስጥ ያከናወነውን ነገር በተመለከተ ያለንን አድናቆት ይጨምርልናል። በተጨማሪም እያንዳንዳችን የመንግሥቱ ታማኝ ተገዢዎች እንድንሆን ያበረታታናል፤ እንዲሁም የ2014 የዓመት ጥቅስ ባለው ትርጉም ላይ እንድናሰላስል ያነሳሳናል።
▪ በወጣትነት ጥበብ የሚንጸባረቅበት ምርጫ ማድረግ
▪ የጭንቀት ጊዜ ከመምጣቱ በፊት ይሖዋን ማገልገል
በሕይወቴ ምን ባደርግ ይሻላል? ራሱን ለይሖዋ የወሰነ ሰው ሁሉ ለዚህ ጥያቄ ትኩረት መስጠት ይኖርበታል። እነዚህ የጥናት ርዕሶች ወጣት ክርስቲያኖች አምላክን በተሟላ መንገድ ማገልገል እንዲችሉ የሚረዷቸውን መሠረታዊ ሥርዓቶች ያብራራሉ፤ በተጨማሪም በዕድሜ የገፉ ክርስቲያኖች አገልግሎታቸውን ማስፋት የሚችሉባቸውን አጋጣሚዎች ይጠቁማሉ።
▪ “መንግሥትህ ይምጣ”—ግን መቼ?
በዛሬው ጊዜ ብዙ ሰዎች በዓለም ሁኔታ ወይም የራሳቸውን ፍላጎት ለማሟላት በሚያደርጉት ጥረት ትኩረታቸው ተከፋፍሏል። ይህ የጥናት ርዕስ የአምላክ መንግሥት በቅርቡ ይህን ክፉ ሥርዓት እንደሚያጠፋ እርግጠኞች እንድንሆን የሚያስችሉ ሦስት ማስረጃዎችን ያብራራል።
ሽፋኑ፦ በለቪፍ ከተማ ወንድሞች ከሌላ አገር ለመጡ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ሲሰብኩ
ዩክሬን
የሕዝብ ብዛት፦
45,561,000
አስፋፊዎች፦
150,887
በ15 ቋንቋዎች 1,737 ጉባኤዎችና 373 ቡድኖች ይመራሉ፤ ከእነዚህ ቋንቋዎች መካከል ሃንጋሪኛ፣ ሩማንያኛ፣ ራሽያኛ፣ የራሽያ ምልክት ቋንቋና ዩክሬንኛ ይገኙበታል