ቲኦክራቲካዊ ዜና
አውስትራሊያ፦ ባለፈው ዓመት ባገኙት ከፍተኛ ቁጥር ላይ 1,541 አስፋፊዎችን በመጨመር የአገልግሎቱን ዓመት በነሐሴ ወር ሲዘጉ 57,272 የሚሆን አዲስ የአስፋፊዎች ከፍተኛ ቁጥር ላይ ደርሰዋል። 31,712 የደረሰ ከምን ጊዜውም የበለጠ ከፍተኛ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናቶች ቁጥር ሪፖርት ተደርጓል።
ቆጵሮስ፦ በነሐሴ ወር 1,433 ሪፖርት ያደረጉ አስፋፊዎች በማግኘት በአገልግሎቱ ዓመት ውስጥ ስምንተኛውን ከፍተኛ የአስፋፊዎች ቁጥር አግኝተዋል። ይህም ካለፈው ዓመት አማካይ ቁጥር 9 በመቶ ጭማሪ ነው።
ዶሜኒካን ሪፑብሊክ፦ በነሐሴ ወር 15,418 የሚሆኑ አስፋፊዎች ሪፖርት በማድረጋቸው ባለፈው የአገልግሎት ዓመት ከነበረው ላይ 20 በመቶ ጭማሪ አግኝተዋል። ከ20 በመቶ በላይ የሚሆኑት አስፋፊዎች በሙሉ ጊዜ አገልግሎት ላይ የተሰማሩ ናቸው።
ጋና፦ በነሐሴ ወር 37,676 አስፋፊዎች የመስክ አገልግሎት ሪፖርት በማድረጋቸው ባለፈው ዓመት በነበረው አማካይ የአስፋፊዎች ቁጥር ላይ የ18 በመቶ ጭማሪ አግኝተዋል።
ፖርቶ ሪኮ፦ በነሐሴ ወር 25,315 የደረሰ አዲስ የአስፋፊዎች ቁጥር ሪፖርት አድርጋለች።
ቶጐ፦ በነሐሴ ወር ባለፈው የአገልግሎት ዓመት በነበረው የአስፋፊዎች ቁጥር ላይ የ28 በመቶ ጭማሪ ላይ ደርሳለች። የአገልግሎቱን ዓመት ሲዘጉ 7,100 ሪፖርት የሚያደርጉ አስፋፊዎች ነበሩ። በዓመቱ ውስጥ 728 አዳዲስ ተጠማቂዎች ነበሩ።