ቲኦክራሲያዊ ዜናዎች
አልባንያ፦ በነሐሴ ወር 600 አስፋፊዎች ሪፖርት አድርገዋል። ይህም በተከታታይ ለ28ኛ ጊዜ የተገኘ ከፍተኛ ቁጥር ነው።
ኢትዮጵያ፦ አዲስ የተቋቋሙ ጉባኤዎች:- ሰሜን አአ፣ አፍንጮ በር አአ፣ ላምበረት አአ፣ ቦዲቲ፣ ደብረ ታቦር።
በጥቅምት በተደረገው መጽሔት የማበርከት ዘመቻ አንዳንድ አስደሳች ውጤቶች ተገኝተዋል:- በደሌ ውስጥ ሁለት አቅኚዎች 58 መጽሔት አበርክተዋል፣ ደብረ ማርቆስ ውስጥ ሦስት አቅኚዎች 77 አበርክተዋል፣ ሐረር ሁለት አቅኚዎች 112 አበርክተዋል፣ ጊምቢ 8 አቅኚዎች 309 አበርክተዋል፣ ጎባ አንድ አቅኚ 40 አበርክቷል፣ አአ ሰፈረሰላም ጉባኤ 10 አቅኚዎች 315 አበርክተዋል፣ አአ አዋሬ ጉባኤ 20 አቅኚዎች 610 ሲያበረክቱ አአ አማኑኤል ጉባኤ 20 አቅኚዎች 737 መጽሔቶች አበርክተዋል። አቅኚዎቹ ይህ ሰው ይወስዳል ይህ አይወስድም እያሉ አስቀድመው ከመፍረድ ይልቅ ለብዙ ሰዎች በተለይ ደግሞ ማንበብ የሚወዱ መስለው ለታዩአቸው ሰዎች መጽሔት እንዲወስዱ ሐሳብ እንደሚያቀርቡላቸው ተናግረዋል።