“ቲኦክራቲካዊ ዜናዎች
ምሥራቅ አፍሪካ፦ በክልላችን ውስጥ በተደረጉት 16 “ብርሃን አብሪዎች” የወረዳ ስብሰባዎች ላይ 37,185 ሰዎች ሲገኙ 1,237 ተጠምቀዋል። ሩዋንዳ ውስጥ ከተጠመቁት 182 ሰዎች ውስጥ 149 የሚሆኑት ረዳት አቅኚዎች ሆነው ለማገልገል ወዲያውኑ አመልክተዋል።
የፈረንሳይ ጊያና፦ የአስፋፊዎች ቁጥር ለ15ኛ ጊዜ ተከታታይ ከፍተኛ ነጥብ ደርሶ 948 አስፋፊዎች ሪፖርት ማድረጋቸውን የጥቅምት ሪፖርት ያሳያል። የጉባኤ አስፋፊዎች የመስክ አገልግሎት አማካይ ሰዓት 15.1 ነበር።
ሆንግ ኮንግ፦ በጥቅምት ወር 2,704 የደረሰ አዲስ ከፍተኛ የአስፋፊዎች ቁጥር ተገኝቷል። እነርሱም 4,043 የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናቶች እንደመሩ ማየት ያስደስታል።
ጃማይካ፦ በጃማይካ ውስጥ የመጀመሪያው የክልል ስብሰባ አዳራሽ ኅዳር 7 ቀን 1992 ተመርቋል። በሥነ ሥርዓቱ ላይ የተገኙ 4,469 ሰዎች ነበሩ።
ማዳጋስካር፦ አምስት “ብርሃን አብሪዎች” የወረዳ ስብሰባዎች ተደርገው 10,694 ሲገኙ 241 ተጠምቀዋል። የተሰብሳቢዎቹ ቁጥር 4,542 ከደረሰው ከፍተኛ የአስፋፊዎች ቁጥር ከሁለት እጥፍ በላይ ነው።