ቲኦክራሲያዊ ዜናዎች
ቦሊቪያ፦ የቅርንጫፍ ቢሮው በጥቅምት ወር 9,588 የደረሰ አዲስ ከፍተኛ የአስፋፊዎች ቁጥር ሪፖርት አድርጓል። በቤት የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፣ በተመላልሶ መጠየቅ፣ በጉባኤ የአስፋፊዎችና በአቅኚዎችም ቁጥር አዲስ ከፍተኛ ቁጥር ላይ ደርሰዋል። እያንዳንዱ የጉባኤ አስፋፊ በአማካይ 14 ሰዓት አገልግሏል።
ህንድ፦ በጥቅምት ወር 13,217 የደረሰ አዲስ ከፍተኛ የአስፋፊዎች ቁጥር ላይ ደርሳለች። ይህ ለሦስተኛ ጊዜ ያገኙት ተከታታይ አዲስ ከፍተኛ ቁጥር ነው።
ኬንያ፦ የመንግሥት አዳራሽ ምረቃዎች:- በጥር 11, 1994 ናይሮቢ ጊቱራይ ሲመረቅ 290 ሰዎች ተገኝተዋል። ባናና ሂል በጥር 29, 1994 ሲመረቅ 248 ሰዎች ተገኝተዋል።
ሊቱዋኒያ፦ የጥቅምት ወር ሪፖርት 871 የደረሰ አዲስ የአስፋፊዎች ቁጥር መገኘቱን ያሳያል። ይህም ከጥቅምት 1992 ጋር ሲወዳደር 39 በመቶ ጭማሪ ነው።