ማስታወቂያዎች
◼ የሚበረከቱ ጽሑፎች ኅዳር፦ የቤተሰብ ኑሮ እና/ወይም ወጣትነትህ የተባሉት መጽሐፎች እያንዳንዳቸው በ3 ብር ይበረከታሉ። ታኅሣሥ፦ ለዘላለም መኖር የተባለው መጽሐፍ ይበረከታል። የቤት የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናቶች ማስጀመርን ግብ በማድረግ የተበረከተላቸውን ሰዎች ሁሉ ተከታትሎ ለመርዳት ልዩ ጥረት ይደረጋል። ጥር፦ ከ1982 በፊት የታተመ በጉባኤው እጅ የሚገኝ ማንኛውም ባለ 192 ገጽ መጽሐፍ (በእንግሊዝኛ የሚገኘው ዘላለማዊ ዓላማ፣ ታላቁን አስተማሪ ማዳመጥ፣ ሕይወት ይህ ብቻ ነውን? የተባለው የእንግሊዝኛ መጽሐፍ የመጀመሪያው እትም) በአንድ ብር ይበረከታል። እነዚህ መጽሐፎች የሌሏቸው ጉባኤዎች የቤተሰብ ኑሮ እና/ወይም ወጣትነትህ የተባሉትን መጽሐፎች እያንዳንዳቸውን በ3 ብር ማበርከት ይችላሉ። የካቲት፦ ራእይ— ታላቁ መደምደሚያ ደርሷል የተባለው መጽሐፍ ሊበረከት ይችላል። ማሳሰቢያ፦ ከላይ የተዘረዘሩትን የዘመቻ ጽሑፎች እስካሁን ያልጠየቁ ጉባኤዎች በቀጣዩ ወር የጽሑፍ ማዘዣ ቅጽ (S-14–AM) መጠየቅ ይችላሉ። በጥር የሚበረከቱት ከ1982 በፊት የታተሙ ጽሑፎች ብሩክሊን አይገኙም።
◼ በእጃችን ያሉ አዳዲስ ጽሑፎች:-
በሥላሴ ማመን ይኖርብሃልን? — አረብኛ
የይሖዋ ምሥክሮችና ትምህርት —እንግሊዝኛ
የ1995 የይሖዋ ምሥክሮች የዓመት መጽሐፍ —እንግሊዝኛ
የመጠበቂያ ግንብ ጥራዝ (1994) —እንግሊዝኛ
የ1995 የይሖዋ ምሥክሮች የዓመት መጽሐፍ —ፈረንሳይኛ