የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • km 12/95 ገጽ 2
  • የታኅሣሥ ወር የአገልግሎት ስብሰባዎች

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • የታኅሣሥ ወር የአገልግሎት ስብሰባዎች
  • የመንግሥት አገልግሎታችን—1995
  • ንዑስ ርዕሶች
  • ታኅሣሥ 4 የሚጀምር ሳምንት
የመንግሥት አገልግሎታችን—1995
km 12/95 ገጽ 2

የታኅሣሥ ወር የአገልግሎት ስብሰባዎች

ታኅሣሥ 4 የሚጀምር ሳምንት

መዝሙር 33

10 ደቂቃ፦ የጉባኤ ማስታወቂያዎች። ከመንግሥት አገልግሎታችን የተመረጡ ማስታወቂያዎች።

15 ደቂቃ፦ “ይሖዋን በየዕለቱ አወድሱት።” በጥያቄና መልስ። አንቀጾቹ ይነበቡ። አንድ ወይም ሁለት አስፋፊዎች መደበኛ ባልሆነ መንገድ ሲያገለግሉ ያጋጠሟቸውን የሚያበረታቱ ተሞክሮዎች ይናገሩ።

20 ደቂቃ፦ “በምድር ላይ በገነት ለዘላለም መኖር ትችላለህ የተባለውን መጽሐፍ ማበርከት።” ይህንን መጽሐፍ በተለይ ቀደም ሲል ስናነጋግራቸው ፍላጎት ላሳዩ ሰዎች የማበርከትን አስፈላጊነት ጠበቅ አድርገህ ግለጽ። የተሰጡትን አቀራረቦች ከልስና በእነዚህ አቀራረቦች አንድ ወይም ሁለት ሠርቶ ማሳያዎች አቅርብ።

መዝሙር 212 እና የመደምደሚያ ጸሎት።

ታኅሣሥ 11 የሚጀምር ሳምንት

መዝሙር 215

8 ደቂቃ፦ የጉባኤ ማስታወቂያዎች። የሒሳብ ሪፖርት። በመስክ አገልግሎት የተሟላና ትርጉም ያለው ተሳትፎ ለማድረግ ዕቅድ ማውጣት ያለብን ለምን እንደሆነ የሚያሳዩ ጥቂት ምክንያቶች አጠር አድርገህ አቅርብ። መስክ ወጥተን አንድ ሰዓት አገልግለን ከመመለስ ይልቅ የሚቻል ከሆነ ለምን ሁለት ሰዓት ወይም ከዚያ በላይ ለማገልገል እቅድ አናወጣም? ብዙውን ጊዜ በአገልግሎታችን ስኬታማ መሆን የምንችለው ለተመላልሶ መጠየቆች ቀደም ብለን የምንዘጋጅና ሁለት ሰዓት ወይም ከዚያ በላይ በመስክ አገልግሎት ለማሳለፍ ዕቅድ ካላቸው አስፋፊዎች ጋር የምናገለግል ከሆነ ነው።

20 ደቂቃ፦ “የመስክ አገልግሎታችንን ሪፖርት ማድረግ ያለብን ለምንና እንዴት ነው?” የጉባኤው ጸሐፊ ሪፖርት ማድረግን በተመለከተ ለጉባኤው በሚስማማ መንገድ አገልግሎታችን በተባለው መጽሐፍ ገጽ 102-110 ላይ የተመሠረተ ማብራሪያ ይሰጣል። ተመላልሶ መጠየቅ ተብለው ሪፖርት ሊደረጉ የሚችሉት የተለያዩ ሁኔታዎች የትኞቹ እንደሆኑ፣ አዲስ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናቶች ሪፖርት የሚደረጉት ከመቼ ጀምሮ እንደሆነ፣ አንድ ወላጅ ልጆቹን መጽሐፍ ቅዱስ ሲያስጠና አንድ ጥናት ብቻ ሪፖርት ማድረግ እንዳለበት (ወላጆች ልጆቻቸውን ሲያስጠኑ አብሮ የሚያጠና ሌላ ሰው በሚኖርበትም ጊዜ እንኳ ይህ ሰው ሁለተኛ ጥናት ተደርጎ ሪፖርት ሊደረግ አይችልም) እና አንድ አስፋፊ ወደ ሌላ ጉባኤ ሲዛወር ምን ማድረግ እንዳለበት ግልጽ አድርግላቸው። ሪፖርት ማድረግን በተመለከተ ያሉትን የተሳሳቱ ሐሳቦች አርም።

17 ደቂቃ፦ “ለጉባኤ ስብሰባዎች መዘጋጀትና ከስብሰባዎቹ መጠቀም።” ንግግርና ውይይት። አንድ ወይም ሁለት አስፋፊዎች ከስብሰባዎች ደስታና ሙሉ ጥቅም እንዲያገኙ ያስቻላቸው ምን ነገር ማድረጋቸው እንደሆነ እንዲናገሩ አድርግ።

መዝሙር 47 እና የመደምደሚያ ጸሎት።

ታኅሣሥ 18 የሚጀምር ሳምንት

መዝሙር 204

10 ደቂቃ፦ የጉባኤ ማስታወቂያዎች። በበዓላት ሰሞን ለሚቀርቡ ሰላምታዎች እንዴት በዘዴ መልስ መስጠት እንደሚቻል ጥቂት ሐሳቦች አቅርብ።

15 ደቂቃ፦ “እድገትህ በግልጽ እንዲታይ አድርግ።” በጥያቄና መልስ።

20 ደቂቃ፦ “ፍላጎት ያሳዩ ሰዎችን ተመልሳችሁ አነጋግሩ።” የተሰጡትን አቀራረቦች ከልስና ሁለት አጠር ያሉ ሠርቶ ማሳያዎች አቅርብ። ሁሉም የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ለማስጀመር ግብ በማድረግ ተመላልሶ መጠየቅ እንዲያደርጉ አበረታታ።

መዝሙር 19 እና የመደምደሚያ ጸሎት።

ታኅሣሥ 25 የሚጀምር ሳምንት

መዝሙር 13

5 ደቂቃ፦ የጉባኤ ማስታወቂያዎች። ከጥር 1 ጀምሮ ስብሰባ የምታደርጉበት ጊዜ የሚለወጥ ከሆነ ወንድሞች አስፈላጊ የሆኑ ማስተካከያዎች በማድረግ ሙሉ ትብብር እንዲያደርጉ አበረታታ።

15 ደቂቃ፦ “ወደ ውጪ አገር የመሄድን ጉዳይ ከተለያዩ አቅጣጫዎች ማገናዘብ” በሚለው ርዕስ ላይ አንድ ሽማግሌ ከአንድ ወጣት ወንድም ጋር ይወያያል። ወጣቱ ወንድም መደምደሚያው ላይ አድናቆቱን ይገልጽና የመንግሥቱ አገልጋዮች ይበልጥ ወደሚያስፈልጉበት ቦታ ተዛውሮ ለማገልገል የይሖዋን እርዳታ ለማግኘት ጥረት እንደሚያደርግ ይናገራል። ወጣቱ ወንድም ምሥጢራዊ ዕቅድ ከማውጣት ይልቅ ያለውን ሐሳብ በግልጽ ስላወያየው ሽማግሌው ያመሰግነዋል።

25 ደቂቃ፦ “ብርሃናችን ሳያቋርጥ እንዲበራ ማድረግ።” ከ1-5 ላይ ያሉትን አንቀጾች አጠር ባለ መንገድ መግቢያ አድርገህ ተጠቀምባቸው። ከ6-16 ያሉት አንቀጾች በጥያቄና መልስ ይሸፈናሉ። አንቀጽ 6-9, 15 እና 16⁠ን አንብብ። ከ17-19 ያሉትን አንቀጾች መደምደሚያ አድርገህ ተጠቀምባቸው። የሚቻል ከሆነ የአገልግሎት የበላይ ተመልካቹ ያቅርበው።

መዝሙር 4 እና የመደምደሚያ ጸሎት።

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ