የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • km 12/98 ገጽ 1
  • የተለየን መሆናችንን ማየት ይችላሉ

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • የተለየን መሆናችንን ማየት ይችላሉ
  • የመንግሥት አገልግሎታችን—1998
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • ልናውጀው የሚገባ መልእክት
    በቲኦክራሲያዊ የአገልግሎት ትምህርት ቤት ከሚሰጠው ሥልጠና ተጠቀም
  • ይሖዋ ድርጅቱን እየመራ ነው
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2020
  • ክርስቲያኖች አምላክን በመንፈስና በእውነት ያመልካሉ
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2002
  • እውነተኛ የክርስቶስ ተከታይ መሆንህን አስመሥክር
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2010
ለተጨማሪ መረጃ
የመንግሥት አገልግሎታችን—1998
km 12/98 ገጽ 1

የተለየን መሆናችንን ማየት ይችላሉ

1 ባለፈው ዓመት ከ300,000 የሚበልጡ አዳዲስ ሰዎች ተጠምቀው ከእኛ ጋር ተቀላቅለዋል። እነዚህ ሰዎች የአምላክ ድርጅት ክፍል ለመሆን እንዲመኙ ያነሳሳቸው በይሖዋ ምሥክሮች ላይ የተመለከቱት ነገር ምንድን ነው? ከሌሎች ሃይማኖቶች ሁሉ የተለየን ሆነን የምንታየው ለምንድን ነው? አንዳንድ ግልጽ መልሶች ቀጥሎ ቀርበዋል:-

—በግል አመለካከታችን ከመመራት ይልቅ መጽሐፍ ቅዱስን በጥብቅ እንከተላለን:- ኢየሱስ ክርስቶስ እንድናደርግ በነገረን መሠረት ይሖዋ አምላክን “በመንፈስና በእውነት” እናመልካለን። ይህ ደግሞ ሃይማኖታዊ ውሸቶችን ማስወገድና በጽሑፍ ከሰፈረው የአምላክ ቃል ጋር መስማማት ማለት ነው።—ዮሐ. 4:23, 24፤ 2 ጢሞ. 3:15–17

—ሰዎች ወደ እኛ እንዲመጡ ከመጠበቅ ይልቅ እነሱ ወደሚገኙበት እንሄዳለን:- ክርስቶስ የሰጠንን የመስበክና የማስተማር ተልዕኮ ተቀብለናል፤ እንዲሁም እርሱ የተወልንን ቅን ልብ ያላቸውን ሰዎች የመፈለግ አርአያ እንከተላለን። እነዚህን ሰዎች በቤታቸው፣ በመንገድ ላይ፣ ወይም በሚገኙበት ቦታ ሁሉ ለማግኘት እንጥራለን።—ማቴ. 9:35፤ 10:11፤ 28:19, 20፤ ሥራ 10:42

—ለሁሉም ሰው ያለ ክፍያ የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት እንሰጣለን:- በየዓመቱ ከአንድ ቢልዮን የሚበልጥ ሰዓት በማሳለፍ ችሎታችንንና ጉልበታችንን አምላክ ለሰጠን አገልግሎት በነፃ እናውላለን። ምንም ሳናዳላ ለሁሉም ዓይነት ሰዎች መጽሐፍ ቅዱስን እናስጠናለን።—ማቴ. 10:8፤ ሥራ 10:34, 35፤ ራእይ 22:17

—ሰዎችን በመንፈሳዊ ለመርዳት የሚያስችል ጥሩ ሥልጠና አግኝተናል:- በግል የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናታችን እንዲሁም በጉባኤ ስብሰባዎችና በትልልቅ ስብሰባዎች ላይ በሚቀርቡልን ትምህርቶች አማካኝነት ለሌሎች መንፈሳዊ እውቀት ለመስጠት የሚያስችለንን በዋጋ ሊተመን የማይችል ቀጣይ ቲኦክራሲያዊ ሥልጠና እናገኛለን።—ኢሳ. 54:13፤ 2 ጢሞ. 2:15፤ 1 ጴጥ. 3:15

—እውነትን በዕለታዊ ሕይወታችን ተግባራዊ በማድረግ በቁም ነገር እንይዛለን:- ለአምላክ ካለን ፍቅር የተነሳ ለውጥ በማድረግ አኗኗራችንን ከእርሱ ፈቃድ ጋር እናስማማለን። የክርስቶስ ዓይነቱ አዲሱ ሰውነት ሌሎች ወደ እውነት እንዲሳቡ ያደርጋቸዋል።—ቆላ. 3:9, 10፤ ያዕ. 1:22, 25፤ 1 ዮሐ. 5:3

—ከሌሎች ጋር በሰላም ለመኖርና ለመሥራት እንጥራለን:- አምላካዊ ባሕርያት ማዳበራችን ድርጊታችንንና አነጋገራችንን እንድንቆጣጠር ይረዳናል። ከሁሉም ሰዎች ጋር ‘ሰላምን እንሻለን፣ እንከተላለንም።’—1 ጴጥ. 3:10, 11፤ ኤፌ. 4:1–3

2 በይሖዋ ድርጅት ውስጥ የሚመለከቱት የክርስቲያናዊ አኗኗር አርአያ ብዙዎች እውነትን እንዲቀበሉ ያነሳሳቸዋል። የእኛም አርአያነት በሚያውቁንና በሚመለከቱን ሰዎች ዘንድ ተመሳሳይ ውጤት እንዲኖረው እንመኛለን።

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ