የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • km 8/00 ገጽ 11
  • ማስታወቂያዎች

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • ማስታወቂያዎች
  • የመንግሥት አገልግሎታችን—2000
የመንግሥት አገልግሎታችን—2000
km 8/00 ገጽ 11

ማስታወቂያዎች

◼ የሚበረከቱ ጽሑፎች ነሐሴ፦ ቀጥሎ ከተዘረዘሩት ባለ 32 ገጽ ብሮሹሮች ማንኛውንም ማበርከት ይቻላል:- አምላክ ስለ እኛ በእርግጥ ያስባልን?፣ በምድር ላይ ለዘላለም በደስታ ኑር!፣ በሥላሴ ማመን ይገባሃልን?፣ ለዘላለም ጸንቶ የሚኖረው መለኮታዊው ስም፣ የአምላክ መንግሥት ገነትን ታመጣለች፣ ስንሞት ምን እንሆናለን?፣ የሕይወት ዓላማ ምንድን ነው?​—⁠እንዴትስ ልታገኘው ትችላለህ?፣ የምትወዱት ሰው ሲሞት፣ ለሰው ሁሉ የሚሆን መጽሐፍ እና የሙታን መናፍስት​—⁠ሊረዱህ ወይም ሊጎዱህ ይችላሉን? ደግሞስ በእርግጥ አሉን? መስከረም፦ በምድር ላይ በገነት ለዘላለም መኖር ትችላለህ። ጥቅምት፦ የመጠበቂያ ግንብ እና የንቁ! መጽሔቶች። ተመላልሶ መጠየቅ የምታደርጉላቸውን ፍላጎት ያሳዩ ሰዎች ኮንትራት ማስገባት ይቻላል። ከወሩ መገባደጃ ጀምሮ “አዲሱ ሺህ ዓመት​—⁠የወደፊቱ ጊዜ ምን ተስፋ ይዞልሃል?” የሚል ርዕስ ያለውን የመንግሥት ዜና ቁጥር 36 ማሰራጨት እንጀምራለን። ኀዳር፦ የመንግሥት ዜና ቁጥር 36 ስርጭት ይቀጥላል። ጉባኤዎች በክልላቸው ውስጥ ለሚገኘው ለእያንዳንዱ የቤት ባለቤት የመንግሥት ዜና ቁጥር 36ን አበርክተው ከጨረሱ አምላክ ከእኛ የሚፈልገው የተባለውን ብሮሹር ወይም እውቀት የተባለውን መጽሐፍ ማበርከት ይችላሉ። የምናነጋግራቸው ሰዎች እነዚህ ጽሑፎች ካሏቸው ለዘላለም መኖር የተባለውን መጽሐፍ ማበርከት ይቻላል።

◼ በዚህ የመንግሥት አገልግሎታችን መጽሔት ገጽ 8 ላይ በመጽሐፍ ጥናት የምናጠናው የዳንኤል መጽሐፍ ፕሮግራም ወጥቷል። ለቀጣዮቹ ጊዜያት ሁሉ መጠቀም ትችሉ ዘንድ ፕሮግራሙን ፎቶ ኮፒ አድርጋችሁ በመጽሐፋችሁ ውስጥ መያዝ ትችላላችሁ።

◼ መስከረም 1 ወይም ከዚያ ብዙም ሳይቆይ ሰብሳቢ የበላይ ተመልካቹ ወይም እርሱ የወከለው ሌላ ወንድም የጉባኤውን ሒሳብ መመርመር ይኖርበታል። የሚቀጥለው የሒሳብ ሪፖርት ከተነበበ በኋላ የሒሳብ ምርመራው ለጉባኤው በማስታወቂያ መነገር አለበት።

◼ ጉባኤዎች በመስከረም ወር በሚልኩት የጽሑፍ ማዘዣ ቅጽ ላይ የ2001 የይሖዋ ምሥክሮች የቀን መቁጠሪያ ማዘዝ መጀመር ይኖርባቸዋል። የቀን መቁጠሪያው በአረብኛ፣ በእንግሊዝኛ፣ በፈረንሳይኛ፣ በሩሲያና በስፓኒሽ ቋንቋዎች ይገኛል።

◼ በ2001 የአገልግሎት ዓመት የምትጠቀሙባቸው በቂ መጠን ያላቸው ቅጾች ለእያንዳንዱ ጉባኤ በመላክ ላይ ናቸው። እባካችሁ እነዚህን ቅጾች በአግባቡ ተጠቀሙባቸው። ለታቀደላቸው ዓላማ ብቻ መዋል ይኖርባቸዋል።

◼ በጉባኤው እጅ ያሉት ጽሑፎችና መጽሔቶች ዓመታዊ ቆጠራ በተቻለ መጠን እስከ ነሐሴ 31, 2000 ባለው ጊዜ ውስጥ መደረግ ይኖርበታል። ይህ ቁጥር በጽሑፍ አስተባባሪው በየወሩ ከሚካሄደው ቆጠራ ጋር ተመሳሳይ ነው። የጽሑፎቹ ጠቅላላ ድምር በጽሑፍ ቆጠራ ቅጽ (S-18-AM) ላይ መሞላት አለበት። በእጅ ያሉ መጽሔቶችን ጠቅላላ ድምር በጽሑፍ ቡድኑ ከታቀፈው ከእያንዳንዱ ጉባኤ የመጽሔት አገልጋይ ማግኘት ይቻላል። እያንዳንዱ አስተባባሪ ጉባኤ ሦስት የጽሑፍ ቆጠራ ቅጾች (S-18-AM) ይደርሱታል። እባካችሁ ዋናውን ቅጂ ከመስከረም 6 በፊት ለማኅበሩ ላኩ። አንድ የካርቦን ቅጂ ፋይላችሁ ውስጥ አስቀምጡ። ሦስተኛው ቅጂ ጊዜያዊ መሥሪያ ሆኖ ሊያገለግል ይችላል። የአስተባባሪ ጉባኤው ጸሐፊ ቆጠራውን በበላይነት መከታተል ይኖርበታል። የአስተባባሪ ጉባኤው ጸሐፊና ሰብሳቢ የበላይ ተመልካች ቅጹ ላይ ይፈርማሉ።

◼ በቅርቡ ይደርሱናል ብለን የምንጠብቃቸው አዳዲስ ጽሑፎች:- አረብኛ፦ የዳንኤል ትንቢት፤ እንግሊዝኛ፦ የ1999 ማውጫ፣ ፈረንሳይኛ፦ የ1999 የመጠበቂያ ግንብ እና ንቁ! ጥራዞች።

◼ እንደገና ይደርሱናል ብለን የምንጠብቃቸው:- እንግሊዝኛ፦ ቅዱስ ጽሑፉ ሁሉ፣ ፍጥረት (ትንሹ)፣ ዲቫይን ጋይዳንስ፣ አዲሲቱ ዓለም ትርጉም:- ዲሉክስ (Dbi12) እና ባለማጣቀሻው መጽሐፍ ቅዱስ (Rbi8)። የቴፕ ክሮች:- ታላቁ ሰው፣ ዓይናችሁ ቀና ይሁን፣ ማቴዎስ፣ የመንግሥቱ ጣዕመ ዜማዎች 1-4፣ የመንግሥቱን መዝሙሮች መዘመር፣ የመንግሥቱ ጣዕመ ዜማዎች ቁጥር 2 በሲዲ።

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ