ማስታወቂያዎች
◼ የሚበረከቱ ጽሑፎች ሰኔ፦ አምላክ ከእኛ የሚፈልገው የተባለው ብሮሹር። ብሮሹሩን ስታበረክቱ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ለማስጀመር ጥረት አድርጉ። ሐምሌ እና ነሐሴ፦ ቀጥሎ ካሉት ባለ 32 ገጽ ብሮሹሮች ውስጥ ማንኛውንም ማበርከት ይቻላል። አምላክ ስለ እኛ በእርግጥ ያስባልን?፣ በምድር ላይ ለዘላለም በደስታ ኑር!፣ በሥላሴ ማመን ይገባሃልን?፣ ለዘላለም ጸንቶ የሚኖረው መለኮታዊው ስም፣ የአምላክ መንግሥት ገነትን ታመጣለች፣ ስንሞት ምን እንሆናለን?፣ የሕይወት ዓላማ ምንድን ነው? እንዴትስ ልታገኘው ትችላለህ? እና የምትወዱት ሰው ሲሞት። መስከረም፦ ጉባኤው ያሉትን እንደ መንግሥትህ ትምጣ እና የአምልኮ አንድነት ያሉ የቆዩ መጽሐፎች።
◼ የይሖዋን ሥልጣን አክብሩ የተሰኘውን የቪዲዮ ፊልም በመስከረም የመንግሥት አገልግሎታችን ላይ እንከልሳለን።
◼ የመንግሥት አዳራሹ እንዳይዘረፍ ሕንጻውን ለቅቆ የሚወጣው የመጨረሻው ሰው በሮቹን መቆለፍና የአጥር ውጪው በር በሚገባ መዘጋቱን ማረጋገጥ አለበት። የበሮቹ ቁልፎች ከሌሉትም ቁልፎቹን የሚይዘውን ወንድም መጥራትና እርሱ እስኪመጣ ድረስ መቆየት አለበት።
◼ አዲስ የደረሱን ጽሑፎች:- እንግሊዝኛ፦ መጽሐፌ የተባለውን መጽሐፍ ማጥኛ ጥያቄዎች፣ የ2003 የመጠበቂያ ግንብ ጥራዝ፤ ፈረንሳይኛ፦ የ2004 የዓመት መጽሐፍ፤ ኦሮምኛ፦ ትራክት ቁጥር 26 “ስለ መጽሐፍ ቅዱስ ይበልጥ ለማወቅ ትፈልጋለህ?”፤ ትግርኛ፦ “ቅዱስ ጽሑፉ ሁሉ” እውነተኛና ጠቃሚ ነው (ጥናት 3)፣ ትራክት ቁጥር 26 “ስለ መጽሐፍ ቅዱስ ይበልጥ ለማወቅ ትፈልጋለህ?”
◼ እንደገና የደረሱን ጽሑፎች:- እንግሊዝኛ፦ የሰው ልጅ አምላክን ለማግኘት ያደረገው ፍለጋ፤ አማርኛ፦ ትራክት ቁጥር 13, 15 እና 16።