የካቲት 15 የሚጀምር ሳምንት
የካቲት 15 የሚጀምር ሳምንት
□ የጉባኤ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፦
lv ምዕ. 9 አን. 13-21፤ በገጽ 104 ላይ የሚገኘው ሣጥን
□ ቲኦክራሲያዊ የአገልግሎት ትምህርት ቤት፦
የመጽሐፍ ቅዱስ ንባብ፦ መሳፍንት 15-18
ቁ. 1፦ መሳፍንት 16:1-12
ቁ. 2፦ ኢየሱስ የጠቀሰው ‘ገሃነመ እሳት’ ምንድን ነው? (rs ገጽ 173 አን. 2 እስከ ገጽ 174 አን. 1)
ቁ. 3፦ ኢየሱስ ዲያብሎስን “የውሸት አባት” ብሎ የጠራው ለምንድን ነው? (ዮሐ. 8:44)
□ የአገልግሎት ስብሰባ፦
5 ደቂቃ፦ ማስታወቂያዎች።
15 ደቂቃ፦ መጠበቂያ ግንብ እና ንቁ! መጽሔቶችን ለማበርከት ዝግጅት አድርጉ። የሚበረከቱትን መጽሔቶች ይዘት በአጭሩ ተናገርና በመጽሔቶቹ ውስጥ ከሚገኙት ርዕሶች መካከል በክልላችሁ ውስጥ የሚገኙ ሰዎችን ሊማርኩ የሚችሉት የትኞቹ እንደሆኑ ጎላ አድርገህ ግለጽ። አንድ አስፋፊ መጽሔቶችን ለማበርከት እንዴት ዝግጅት ማድረግ እንደሚቻል የሚያሳይ መነባነብ እንዲያቀርብ አድርግ። አስፋፊው ለክልሉ ይበልጥ ተስማሚ የሆኑት ርዕሶች የትኞቹ እንደሆኑ ይወስናል፣ አንድ ጥያቄ ያዘጋጃል እንዲሁም የሚያነባቸውን ጥቅሶች ይመርጣል። ከዚያም እያንዳንዱን መጽሔት እንዴት እንደሚያበረክት እየተለማመደ ዝግጅት ያደርጋል።
15 ደቂቃ፦ “መጥተህ ተከታዬ ሁን።” በጥያቄና መልስ የሚቀርብ። ከውይይቱ በኋላ በአገልግሎት ትምህርት ቤት መጽሐፍ ገጽ 70 ላይ የሚገኘውን ሐሳብ ተጠቅመህ በጉባኤ ስብሰባዎች ላይ ሐሳብ ስለመስጠት ተገቢ የሆኑ ማሳሰቢያዎችን ስጥ።