ሐምሌ 25 የሚጀምር ሳምንት
ሐምሌ 25 የሚጀምር ሳምንት
መዝሙር 17 እና ጸሎት
□ የጉባኤ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፦
dp ምዕ. 15 አን. 1-9 (25 ደቂቃ)
□ ቲኦክራሲያዊ የአገልግሎት ትምህርት ቤት፦
የመጽሐፍ ቅዱስ ንባብ፦ መዝሙር 79-86 (10 ደቂቃ)
ቁ. 1፦ መዝሙር 84:1 እስከ 85:7 (4 ደቂቃ ወይም ከዚያ በታች)
ቁ. 2፦ የአምላክ መንግሥት ፍጥረታት ሁሉ በአንድ ንጹሕ አምልኮ እንዲጠቃለሉ ያደርጋል—rs ገጽ 228 አን. 4 እስከ ገጽ 229 አን. 1 (5 ደቂቃ)
ቁ. 3፦ በአምላክ መኖር የማያምን ጋኔን የለም የምንለው ለምንድን ነው?—ያዕ. 2:19 (5 ደቂቃ)
□ የአገልግሎት ስብሰባ፦
5 ደቂቃ፦ ማስታወቂያዎች። በነሐሴ ወር የሚበረከተውን ጽሑፍ ከተናገርክ በኋላ አንድ ሠርቶ ማሳያ እንዲቀርብ አድርግ።
10 ደቂቃ፦ የጤና እክል እያለባቸውም በስብከቱ ሥራ ተካፍለዋል። በ2011 የዓመት መጽሐፍ (እንግሊዝኛ) ገጽ 64 አንቀጽ 1-2 እና ገጽ 69 አንቀጽ 1 ላይ ተመሥርቶ በውይይት የሚቀርብ። አድማጮች ከእያንዳንዱ ተሞክሮ ምን ትምህርት እንዳገኙ ሐሳብ እንዲሰጡ ጋብዝ።
20 ደቂቃ፦ “ብዙ ዓይነት ሰዎችን እንዲማርኩ ተደርገው የተዘጋጁት መጽሔቶቻችን።” በጥያቄና መልስ የሚቀርብ። አንቀጽ 2ን ከተወያያችሁ በኋላ በቅርቡ የወጣውን የንቁ! መጽሔት ይዘት በአንድ ደቂቃ ውስጥ ተናገር። አድማጮች፣ ውይይት ለመጀመር ምን ጥያቄ ማንሳት እንዲሁም የትኛውን ጥቅስ ማንበብ እንደሚችሉ ጠይቅ፤ እንዲሁም ንቁ! መጽሔቱን እንዴት ማበርከት እንደሚቻል የሚያሳይ ሠርቶ ማሳያ እንዲቀርብ አድርግ። በአንቀጽ 3 ላይ ከተወያያችሁ በኋላ፣ ከላይ በቀረበው መመሪያ መሠረት በቅርቡ የወጣውን መጠበቂያ ግንብ አስተዋውቅ።
መዝሙር 55 እና ጸሎት