ጥቅምት 31 የሚጀምር ሳምንት ፕሮግራም
ጥቅምት 31 የሚጀምር ሳምንት
መዝሙር 9 እና ጸሎት
□ የጉባኤ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፦
fy ምዕ. 1 ከአን. 8-14 (25 ደቂቃ)
□ ቲኦክራሲያዊ የአገልግሎት ትምህርት ቤት፦
የመጽሐፍ ቅዱስ ንባብ፦ ምሳሌ 22-26 (10 ደቂቃ)
የቲኦክራሲያዊ አገልግሎት ትምህርት ቤት ክለሳ (20 ደቂቃ)
□ የአገልግሎት ስብሰባ፦
10 ደቂቃ፦ ማስታወቂያዎች። “ጽሑፎቼ በምን ዓይነት ሁኔታ ላይ ይገኛሉ?” በንግግር የሚቀርብ። ከንግግሩ በኋላ በገጽ 8 ላይ የሚገኘውን የአቀራረብ ናሙና በመጠቀም በኅዳር ወር የመጀመሪያው ቅዳሜ እንዴት ጥናት ማስጀመር እንደሚቻል የሚያሳይ ሠርቶ ማሳያ እንዲቀርብ አድርግ።
15 ደቂቃ፦ በአገልግሎት ላይ ንጹሕና ሥርዓታማ መሆን ያለው ጥቅም። በአገልግሎት ትምህርት ቤት መጽሐፍ ከገጽ 131 እስከ ገጽ 134 ባለው ሐሳብ ላይ ተመሥርቶ በውይይት የሚቀርብ።
10 ደቂቃ፦ በኅዳር ወር መጽሔቶችን ለማበርከት ዝግጅት አድርጉ። በውይይት የሚቀርብ። በአንድ ወይም በሁለት ደቂቃ ውስጥ በክልላችሁ ውስጥ ያሉ ሰዎችን ትኩረት ሊስቡ የሚችሉ አንዳንድ ርዕሶችን መርጠህ ተናገር። ከዚያም በመጠበቂያ ግንብ መጽሔት የሽፋን ርዕስ ዙሪያ የሰዎችን የማወቅ ፍላጎት ለመቀስቀስ ምን ጥያቄ ማንሳት እንዲሁም የትኞቹን ጥቅሶች ማንበብ እንደሚቻል እንዲናገሩ አድማጮችን ጠይቅ። በንቁ! መጽሔት የሽፋን ርዕስ ዙሪያም ተመሳሳይ ጥያቄዎች አቅርብ፤ ጊዜ ካለህ አንድ ተጨማሪ ርዕስ ማከል ትችላለህ። እያንዳንዱን መጽሔት እንዴት ማበርከት እንደሚቻል የሚያሳይ ሠርቶ ማሳያ እንዲቀርብ አድርግ።
መዝሙር 4 እና ጸሎት