ሐምሌ 16 የሚጀምር ሳምንት ፕሮግራም
ሐምሌ 16 የሚጀምር ሳምንት
መዝሙር 10 እና ጸሎት
□ የጉባኤ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፦
fy ምዕ. 12 ከአን. 1-8 (25 ደቂቃ)
□ ቲኦክራሲያዊ የአገልግሎት ትምህርት ቤት፦
የመጽሐፍ ቅዱስ ንባብ፦ ሕዝቅኤል 15-17 (10 ደቂቃ)
ቁ. 1፦ ሕዝቅኤል 16:14-27 (4 ደቂቃ ወይም ከዚያ በታች)
ቁ. 2፦ ኢየሱስ በዮሐንስ 18:37 ላይ የጠቀሰው እውነት ምንድን ነው? (5 ደቂቃ)
ቁ. 3፦ ኢየሱስ የቁርባንን ሥርዓት አቋቁሟል?—rs ከገጽ 263 አን. 2 እስከ ገጽ 265 አን. 2 (5 ደቂቃ)
□ የአገልግሎት ስብሰባ፦
5 ደቂቃ፦ ማስታወቂያዎች።
10 ደቂቃ፦ በአገልግሎታችሁ ይበልጥ ውጤታማ እንድትሆኑ በቲኦክራሲያዊ የአገልግሎት ትምህርት ቤት ተጠቀሙ። በአገልግሎት ትምህርት ቤት መጽሐፍ ከገጽ 6 አንቀጽ 1 እስከ ገጽ 8 መጨረሻ ድረስ ባለው ሐሳብ ላይ ተመሥርቶ የቲኦክራሲያዊ የአገልግሎት ትምህርት ቤት የበላይ ተመልካቹ በንግግር የሚያቀርበው። ትምህርት ቤቱ ከአገልግሎት ጋር በተያያዘ እንዴት እንደጠቀማቸው እንዲናገሩ ለአንድ ወይም ለሁለት አስፋፊዎች ቃለ ምልልስ አድርግ።
20 ደቂቃ፦ “ሰዎች አምላክን እንዲሰሙ እርዷቸው።” በጥያቄና መልስ የሚቀርብ። አንቀጽ 5 ላይ ስትወያዩ ከሁለቱ ብሮሹሮች አንዱን እንዴት ማበርከት እንደሚቻል የሚያሳይ ሠርቶ ማሳያ እንዲቀርብ አድርግ። አንቀጽ 6 ላይ ከተወያያችሁ በኋላ ደግሞ አንድ አስፋፊ አምላክን ስማ የተባለውን ብሮሹር ተጠቅሞ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ሲመራ የሚያሳይ ሦስት ደቂቃ የሚወስድ ሠርቶ ማሳያ እንዲቀርብ አድርግ፤ አስፋፊው በብሮሹሩ ገጽ 4 ላይ በሚገኘው የመጀመሪያ ሥዕላዊ መግለጫ ተጠቅሞ ጥናቱን ያወያየዋል።
መዝሙር 6 እና ጸሎት