የካቲት 4 የሚጀምር ሳምንት ፕሮግራም
የካቲት 4 የሚጀምር ሳምንት
መዝሙር 42 እና ጸሎት
□ የጉባኤ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፦
cf ምዕ. 1 ከአን. 1-7 (30 ደቂቃ)
□ ቲኦክራሲያዊ የአገልግሎት ትምህርት ቤት፦
የመጽሐፍ ቅዱስ ንባብ፦ ማቴዎስ 22-25 (10 ደቂቃ)
ቁ. 1፦ ማቴዎስ 23:25-39 (4 ደቂቃ ወይም ከዚያ በታች)
ቁ. 2፦ ክርስቲያኖች የመጽሐፍ ቅዱስን ትንቢቶች በጉጉት መከታተል የሚገባቸው ለምንድን ነው?—rs ገጽ 296 አን. 7 እስከ ገጽ 297 አን. 4 (5 ደቂቃ)
ቁ. 3፦ በምሳሌ 3:5 ላይ የሚገኘው ምክር ጥበብ ያዘለ እንደሆነ የሚያሳዩት የትኞቹ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ምሳሌዎች ናቸው? (5 ደቂቃ)
□ የአገልግሎት ስብሰባ፦
10 ደቂቃ፦ በየካቲት ወር መጽሔቶችን ለማበርከት የሚረዱ ሐሳቦች። በውይይት የሚቀርብ። መጽሔቶቹ በክልላችሁ ውስጥ ያሉ ሰዎችን ትኩረት ሊስቡ የሚችሉበትን ምክንያት ከ30 እስከ 60 ሴኮንድ ባለው ጊዜ ውስጥ ተናገር። ከዚያም በመጠበቂያ ግንብ መጽሔት የሽፋን ርዕሰ ጉዳይ ዙሪያ የሰዎችን የማወቅ ፍላጎት ለመቀስቀስ ምን ጥያቄ ማንሳት እንዳሰቡ አድማጮችን ጠይቅ፤ በመቀጠልም የትኞቹን ጥቅሶች ማንበብ እንዳሰቡ ጠይቅ። በንቁ! መጽሔት የሽፋን ርዕሰ ጉዳይ ዙሪያም በተመሳሳይ መንገድ ጥያቄዎችን አቅርብ፤ ጊዜ ካለህ ከመጠበቂያ ግንብ ወይም ከንቁ! መጽሔት አንድ ተጨማሪ ርዕስ ማከል ትችላለህ። እያንዳንዱን መጽሔት እንዴት ማበርከት እንደሚቻል የሚያሳይ ሠርቶ ማሳያ እንዲቀርብ አድርግ።
10 ደቂቃ፦ አንድ ሰው እንዲህ ቢልስ፦ ‘በአምላክ አላምንም።’ በማመራመር መጽሐፍ ከገጽ 151 አንቀጽ 1 እስከ ገጽ 152 አንቀጽ 1 ባለው ሐሳብ ላይ ተመሥርቶ በውይይት የሚቀርብ። አንድ አጠር ያለ ሠርቶ ማሳያ እንዲቀርብ አድርግ።
10 ደቂቃ፦ ለጉባኤው እንደሚያስፈልግ ተጠቀሙበት።
መዝሙር 1 እና ጸሎት