ሰኔ 17 የሚጀምር ሳምንት ፕሮግራም
ሰኔ 17 የሚጀምር ሳምንት
መዝሙር 48 እና ጸሎት
□ የጉባኤ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፦
cf ምዕ. 7 ከአን. 9-16 (30 ደቂቃ)
□ ቲኦክራሲያዊ የአገልግሎት ትምህርት ቤት፦
የመጽሐፍ ቅዱስ ንባብ፦ የሐዋርያት ሥራ 5-7 (10 ደቂቃ)
ቁ. 1፦ የሐዋርያት ሥራ 5:17-32 (4 ደቂቃ ወይም ከዚያ በታች)
ቁ. 2፦ አንድ ሰው በይሖዋ ዘንድ ለመታወቅ ምን ማድረግ ይኖርበታል?—2 ጢሞ. 2:19 (5 ደቂቃ)
ቁ. 3፦ ከኢየሱስ መሥዋዕት ዘላቂ ጥቅም ለማግኘት ምን ማድረግ ይኖርብናል?—rs ገጽ 310 አን. 2-3 (5 ደቂቃ)
□ የአገልግሎት ስብሰባ፦
10 ደቂቃ፦ በአገልግሎት ላይ ለሰዎች አክብሮት እንዳለን ማሳየት የምንችለው እንዴት ነው? በአገልግሎት ትምህርት ቤት መጽሐፍ ከገጽ 190 አንቀጽ 1 እስከ ገጽ 192 አንቀጽ 1 ባለው ሐሳብ ላይ ተመሥርቶ በውይይት የሚቀርብ። አንድ አስፋፊ የቤቱን ባለቤት አክብሮት በጎደለው መንገድ ሲያናግረው የሚያሳይ ከእውነታው ያልራቀ አጭር ሠርቶ ማሳያ እንዲቀርብ አድርግ። ከዚያም ሠርቶ ማሳያው በድጋሚ እንዲታይ አድርግ፤ በዚህ ጊዜ አስፋፊው ለሚያነጋግረው ሰው ተገቢውን አክብሮት ያሳያል።
10 ደቂቃ፦ ጥናታችሁ አስፋፊ እንዲሆን እርዱት። የተደራጀ ሕዝብ በተባለው መጽሐፍ ከገጽ 78 አንቀጽ 3 አንስቶ ገጽ 80 ላይ እስከተጠቀሰው የመጨረሻ ነጥብ ድረስ ባለው ሐሳብ ላይ ተመሥርቶ በውይይት የሚቀርብ።
10 ደቂቃ፦ “ይሖዋን ለማወደስ የሚያስችሉ ተጨማሪ አጋጣሚዎች።” በጥያቄና መልስ የሚቀርብ። የወረዳ የበላይ ተመልካቹ ጉባኤውን በጎበኘበት ወር ላይ ረዳት አቅኚ ሆነው ላገለገሉ አንድ ወይም ሁለት አስፋፊዎች ቃለ ምልልስ አድርግ።
መዝሙር 9 እና ጸሎት