ማስታወቂያዎች
◼ የሚበረከቱ ጽሑፎች፦ ሰኔ፦ ከሚከተሉት ትራክቶች አንዱን ማበርከት ትችላላችሁ፦ በቤተሰብ ኑሮ ተደሰት፣ ዓለምን የሚገዛው ማን ነው? መጽሐፍ ቅዱስን ማመን የሚችሉት ለምንድን ነው? ወይም እውነቱን ማወቅ ትፈልጋለህ? ግለሰቡ ፍላጎት ካለው የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት በተባለው መጽሐፍ አሊያም አምላክን ስማ ወይም አምላክን ስማ የዘላለም ሕይወት ታገኛለህ በተባለው ብሮሹር ተጠቅማችሁ መጽሐፍ ቅዱስን እንዴት ማጥናት እንደሚችል ልታሳዩት ትችላላችሁ። ሐምሌ እና ነሐሴ፦ ከአምላክ የተላከ ምሥራች! የተባለውን ወይም ሌላ ማንኛውም ብሮሹር። መስከረም፦ መጠበቂያ ግንብ እና ንቁ! መጽሔቶች።