ጥቅምት 7 የሚጀምር ሳምንት ፕሮግራም
ጥቅምት 7 የሚጀምር ሳምንት
መዝሙር 47 እና ጸሎት
□ የጉባኤ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፦
cf ምዕ. 12 ከአን. 15-21 እና ሣጥን (30 ደቂቃ)
□ ቲኦክራሲያዊ የአገልግሎት ትምህርት ቤት፦
የመጽሐፍ ቅዱስ ንባብ፦ ኤፌሶን 1-6 (10 ደቂቃ)
ቁ. 1፦ ኤፌሶን 4:1-16 (4 ደቂቃ ወይም ከዚያ በታች)
ቁ. 2፦ ከሁሉ አስቀድሞ የአምላክን ጽድቅ መፈለግ ሲባል ምን ማለት ነው?—ማቴ. 6:33 (5 ደቂቃ)
ቁ. 3፦ ሁሉም ሃይማኖት የራሱ ጥሩ ጎን አለው የሚባለው እውነት ነው?—rs ገጽ 322 አን. 3 እስከ ገጽ 323 አን. 1 (5 ደቂቃ)
□ የአገልግሎት ስብሰባ፦
10 ደቂቃ፦ በጥቅምት ወር መጽሔቶችን ለማበርከት የሚረዱ ሐሳቦች። በውይይት የሚቀርብ። መጽሔቶቹ በክልላችሁ ውስጥ ያሉ ሰዎችን ትኩረት ሊስቡ የሚችሉበትን ምክንያት ከ30 እስከ 60 ሴኮንድ ባለው ጊዜ ውስጥ ተናገር። ከዚያም በመጠበቂያ ግንብ መጽሔት የሽፋን ርዕሰ ጉዳይ ዙሪያ የሰዎችን የማወቅ ፍላጎት ለመቀስቀስ ምን ጥያቄ ማንሳት እንዳሰቡ አድማጮችን ጠይቅ፤ በመቀጠልም የትኞቹን ጥቅሶች ማንበብ እንዳሰቡ ጠይቅ። በንቁ! መጽሔት የሽፋን ርዕሰ ጉዳይ ዙሪያም በተመሳሳይ መንገድ ጥያቄዎችን አቅርብ፤ ጊዜ ካለህ ከመጠበቂያ ግንብ ወይም ከንቁ! መጽሔት አንድ ተጨማሪ ርዕስ ማከል ትችላለህ። እያንዳንዱን መጽሔት እንዴት ማበርከት እንደሚቻል የሚያሳይ ሠርቶ ማሳያ እንዲቀርብ አድርግ።
10 ደቂቃ፦ ለጉባኤው እንደሚያስፈልግ ተጠቀሙበት።
10 ደቂቃ፦ በትጋት እየሠሩ ያሉት። (1 ተሰ. 5:12, 13) ለሁለት ሽማግሌዎች ቃለ ምልልስ አድርግ። በጉባኤ ውስጥ እና ከዚያ ውጭ ያላቸው ቲኦክራሲያዊ ኃላፊነቶች ምንድን ናቸው? ሰብዓዊ ሥራ እየሠሩና የቤተሰብ ኃላፊነት እያለባቸው እነዚህን ቲኦክራሲያዊ ኃላፊነቶቻቸውን ሊወጡ የቻሉት እንዴት ነው? ለአገልግሎታቸው ቅድሚያውን የሚሰጡት እንዴት ነው? የቤተሰባቸው አባላት ድጋፍ የሚያደርጉላቸው እንዴት ነው?
መዝሙር 42 እና ጸሎት