የካቲት 24 የሚጀምር ሳምንት ፕሮግራም
የካቲት 24 የሚጀምር ሳምንት
መዝሙር 10 እና ጸሎት
□ የጉባኤ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፦
jl ትምህርት 3-4 (30 ደቂቃ)
□ ቲኦክራሲያዊ የአገልግሎት ትምህርት ቤት፦
የመጽሐፍ ቅዱስ ንባብ፦ ዘፍጥረት 32-35 (10 ደቂቃ)
የቲኦክራሲያዊ የአገልግሎት ትምህርት ቤት ክለሳ (20 ደቂቃ)
□ የአገልግሎት ስብሰባ፦
5 ደቂቃ፦ በመጀመሪያው ቅዳሜ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ማስጀመር። በንግግር የሚቀርብ። በመጋቢት ወር የመጀመሪያ ቅዳሜ ጉባኤው ለመስክ አገልግሎት ያደረገውን ዝግጅት ጥቀስ። በገጽ 4 ላይ የሚገኘውን የአቀራረብ ናሙና በመጠቀም ሠርቶ ማሳያ እንዲቀርብ አድርግ።
15 ደቂቃ፦ መጽናት ያለው ጥቅም። በ2013 የዓመት መጽሐፍ (እንግሊዝኛ) ከገጽ 45 አንቀጽ 1 እስከ ገጽ 46 አንቀጽ 1 እንዲሁም ከገጽ 136-137 ላይ ተመሥርቶ በውይይት የሚቀርብ። ምን ትምህርት እንዳገኙ አድማጮችን ጠይቅ።
10 ደቂቃ፦ “ሰዎች በመታሰቢያው በዓል ላይ እንዲገኙ የምንጋብዝበት ዘመቻ መጋቢት 22 ይጀምራል።” በአገልግሎት የበላይ ተመልካቹ የሚቀርብ ንግግር። የመታሰቢያው በዓል የመጋበዣ ወረቀት አንድ ቅጂ እንዲታደል ካደረግህ በኋላ ስለ ይዘቱ ተናገር። ዘመቻውን የተመለከተ መመሪያ ከያዘው ለሽማግሌዎች የተላከ ደብዳቤ ላይ ተግባራዊ ሊሆኑ የሚችሉ ነጥቦችን ጥቀስ፤ እንዲሁም የጉባኤውን ክልል ለመሸፈን ስለተደረገው ዝግጅት ተናገር።
መዝሙር 5 እና ጸሎት