ጥቅምት 20 የሚጀምር ሳምንት ፕሮግራም
ጥቅምት 20 የሚጀምር ሳምንት
መዝሙር 5 እና ጸሎት
የጉባኤ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፦
bt ምዕ. 9 ከአን. 1-7፣ በገጽ 68 ላይ የሚገኘው የመግቢያ ሐሳብ እና በገጽ 70 ላይ የሚገኝ ሣጥን (30 ደቂቃ)
ቲኦክራሲያዊ የአገልግሎት ትምህርት ቤት፦
የመጽሐፍ ቅዱስ ንባብ፦ ዘዳግም 7-10 (10 ደቂቃ)
ቁ. 1፦ ዘዳግም 9:15-29 (4 ደቂቃ ወይም ከዚያ በታች)
ቁ. 2፦ ፍጹም ሰው ኃጢአት ሊሠራ የሚችለው እንዴት ነው?—rs ገጽ 370 አን. 1 እስከ ገጽ 371 አን. 1 (5 ደቂቃ)
ቁ. 3፦ አዶንያስ—የይሖዋን ውሳኔዎች ተቀበሉ—w05 7/1 ገጽ 28 አን. 5 እስከ ገጽ 29 አን. 1 (5 ደቂቃ)
የአገልግሎት ስብሰባ፦
15 ደቂቃ፦ “ስለ 1914 ያለንን እምነት ማስረዳት።” በውይይት የሚቀርብ። አድማጮች በተዘረዘሩት ነጥቦች ላይ ሐሳብ እንዲሰጡ ጋብዝ።
15 ደቂቃ፦ ስለ 1914 ያለንን እምነት ለማስረዳት የሚረዳ መሣሪያ። የሰባት ደቂቃ ሠርቶ ማሳያ እንዲቀርብ በማድረግ ክፍሉን ጀምር፤ በሠርቶ ማሳያው ላይ አንድ አስፋፊ በኅዳር 1, 2014 መጠበቂያ ግንብ ገጽ 11 ላይ ያለውን ሠንጠረዥ ተጠቅሞ በዳንኤል ምዕራፍ 4 ላይ የሚገኘው ትንቢት ከአምላክ መንግሥት ጋር ያለውን ግንኙነት ለመጽሐፍ ቅዱስ ተማሪው በአጭሩ ያብራራል። ሠርቶ ማሳያው ውጤታማ የሆነበትን ምክንያት አስመልክቶ ሐሳብ እንዲሰጡ አድማጮችን ጋብዝ። ራእይ 12:10, 12ን አንብብ፤ ከዚያም የአምላክ መንግሥት በ1914 መግዛት እንደጀመረ ማወቃችን ምሥራቹን በጥድፊያ ስሜት እንድንሰብክ የሚያነሳሳን እንዴት እንደሆነ አድማጮች ሐሳብ እንዲሰጡ በመጋበዝ ክፍሉን ደምድም።
መዝሙር 49 እና ጸሎት