ሚያዝያ 6 የሚጀምር ሳምንት ፕሮግራም
ሚያዝያ 6 የሚጀምር ሳምንት
መዝሙር 124 እና ጸሎት
የጉባኤ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፦
bt ምዕ. 17 ከአን. 1-7 (30 ደቂቃ)
ቲኦክራሲያዊ የአገልግሎት ትምህርት ቤት፦
የመጽሐፍ ቅዱስ ንባብ፦ 1 ሳሙኤል 16-18 (8 ደቂቃ)
ቁ. 1፦ 1 ሳሙኤል 18:17-24 (3 ደቂቃ ወይም ከዚያ በታች)
ቁ. 2፦ በሰዎች ላይ ለሚደርሰው መከራና ሥቃይ ተጠያቂው አምላክ ነው?—nwt ገጽ 18 አን. 1-4 (5 ደቂቃ)
ቁ. 3፦ ባርቅ—ጭብጥ፦ ደፋር ሁኑ፤ በይሖዋም ታመኑ—w03 11/15 ገጽ 28 አን. 5 እስከ ገጽ 31 (5 ደቂቃ)
የአገልግሎት ስብሰባ፦
የወሩ ጭብጥ፦ ‘ለመልካም ሥራ ሁሉ ዝግጁ ሁኑ።’—ቲቶ 3:1
10 ደቂቃ፦ በሚያዝያ ወር መጽሔቶችን አበርክቱ። በውይይት የሚቀርብ። በቅድሚያ፣ የተዘጋጁትን የአቀራረብ ናሙናዎች በመጠቀም እያንዳንዱን መጽሔት እንዴት ማበርከት እንደሚቻል የሚያሳዩ ሠርቶ ማሳያዎች እንዲቀርቡ አድርግ። ከዚያም እያንዳንዱን የአቀራረብ ናሙና ከመክፈቻው ሐሳብ ጀምሮ እስከ መደምደሚያው ድረስ ተራ በተራ ተወያዩበት።
10 ደቂቃ፦ ምን ውጤት አገኘን? በውይይት የሚቀርብ። አስፋፊዎች “በአገልግሎት ረገድ ክህሎታችንን ማዳበር—የመጽሔት ደንበኞች ማፍራት” በሚለው ርዕስ ላይ የቀረቡትን ነጥቦች ተግባራዊ በማድረጋቸው ምን ጥቅም እንዳገኙ ሐሳብ እንዲሰጡ ጠይቃቸው። እንዲሁም ያገኙትን ግሩም ተሞክሮ እንዲናገሩ ጋብዝ።
10 ደቂቃ፦ ለጉባኤው እንደሚያስፈልግ ተጠቀሙበት።
መዝሙር 106 እና ጸሎት