ጥቅምት 5 የሚጀምር ሳምንት ፕሮግራም
ጥቅምት 5 የሚጀምር ሳምንት
መዝሙር 13 እና ጸሎት
የጉባኤ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፦
bt ምዕ. 25 ከአን. 8-13 እና በገጽ 201 ላይ የሚገኝ ሣጥን (30 ደቂቃ)
ቲኦክራሲያዊ የአገልግሎት ትምህርት ቤት፦
የመጽሐፍ ቅዱስ ንባብ፦ 1 ዜና መዋዕል 1-4 (8 ደቂቃ)
ቁ. 1፦ 1 ዜና መዋዕል 1:28-42 (3 ደቂቃ ወይም ከዚያ በታች)
ቁ. 2፦ ዔሊ—ጭብጥ፦ ልል መሆን አምላክን ያሰድባል—w10 10/1 ከገጽ 15 አን. 4 እስከ ገጽ 16 አን. 5 (5 ደቂቃ)
ቁ. 3፦ “ፀረ ክርስቶስ” የሚለው መጠሪያ የሚያመለክተው ማንን ነው?—የቃላት መፍቻ፣ nwt ገጽ 1654 (5 ደቂቃ)
የአገልግሎት ስብሰባ፦
የወሩ ጭብጥ፦ ‘ምሥራቹን በተሟላ ሁኔታ መሥክሩ።’ —ሥራ 20:24
10 ደቂቃ፦ በጥቅምት ወር መጽሔቶችን አበርክቱ። በውይይት የሚቀርብ። በቅድሚያ በዚህ ገጽ ላይ የሚገኙትን የአቀራረብ ናሙናዎች በመጠቀም መጽሔቶቹን እንዴት ማበርከት እንደሚቻል የሚያሳዩ ሁለት ሠርቶ ማሳያዎች እንዲቀርቡ አድርግ። ከዚያም በአቀራረብ ናሙናዎቹ ውስጥ የሰፈረውን እያንዳንዱን ሐሳብ ተራ በተራ ተወያዩበት።
10 ደቂቃ፦ ለጉባኤው እንደሚያስፈልግ ተጠቀሙበት።
10 ደቂቃ፦ ምን ውጤት አገኘን? በውይይት የሚቀርብ። አስፋፊዎች “በአገልግሎት ረገድ ክህሎታችንን ማዳበር—በንግድ አካባቢዎች መመሥከር” በሚለው ርዕስ ላይ የቀረቡትን ነጥቦች ተግባራዊ በማድረጋቸው ምን ጥቅም እንዳገኙ ሐሳብ እንዲሰጡ ጠይቃቸው። እንዲሁም ያገኙትን የሚያበረታታ ተሞክሮ እንዲናገሩ ጋብዝ።
መዝሙር 98 እና ጸሎት