ከሐምሌ 22-28
መዝሙር 66–68
መዝሙር 7 እና ጸሎት | የመግቢያ ሐሳብ (1 ደቂቃ)
1. ይሖዋ ሸክማችንን በየዕለቱ ይሸከምልናል
(10 ደቂቃ)
ይሖዋ ጸሎታችንን ይሰማል፤ መልስም ይሰጠናል (መዝ 66:19፤ w23.05 12 አን. 15)
ይሖዋ የተቸገሩ ሰዎች ለሚያስፈልጋቸው ነገር ትኩረት ይሰጣል (መዝ 68:5፤ w10 12/1 23 አን. 6፤ w09 4/1 31 አን. 1)
ይሖዋ በየዕለቱ ይረዳናል (መዝ 68:19፤ w23.01 19 አን. 17)
ለማሰላሰል የሚረዳ ጥያቄ፦ ይሖዋ ሸክማችንን እንዲሸከምልን መፍቀድ የምንችለው እንዴት ነው?
2. መንፈሳዊ ዕንቁዎች
(10 ደቂቃ)
መዝ 68:18—በጥንቷ እስራኤል ዘመን ‘እንደ ስጦታ የሆኑ ሰዎች’ የተባሉት እነማን ናቸው? (w06 6/1 10 አን. 5)
ከዚህ ሳምንት የመጽሐፍ ቅዱስ ንባብ ምን መንፈሳዊ ዕንቁዎች አግኝታችኋል?
3. የመጽሐፍ ቅዱስ ንባብ
(4 ደቂቃ) መዝ 66:1-20 (th ጥናት 11)
4. ውይይት መጀመር
(3 ደቂቃ) ከቤት ወደ ቤት። የቤቱ ባለቤት ከአንተ የተለየ ባሕል አለው። (lmd ምዕራፍ 5 ነጥብ 3)
5. ተመላልሶ መጠየቅ
(4 ደቂቃ) ከቤት ወደ ቤት። ባለፈው ውይይታችሁ ወቅት ባበረከትከው ትራክት ላይ ተመሥርተህ ውይይቱን ቀጥል። (lmd ምዕራፍ 9 ነጥብ 3)
6. ደቀ መዛሙርት ማድረግ
(5 ደቂቃ) lff ምዕራፍ 15 ማስተዋወቂያ እና ነጥብ 1-3 (th ጥናት 8)
መዝሙር 102
7. የወንድምህን ሸክም ማቅለል ትችል ይሆን?
(15 ደቂቃ) ውይይት።
የአምላክ አገልጋዮች የሕይወትን ውጣ ውረድ ብቻቸውን መጋፈጥ አያስፈልጋቸውም። (2ዜና 20:15፤ መዝ 127:1) ይሖዋ ይረዳናል። (ኢሳ 41:10) ይሖዋ የሚረዳን በየትኞቹ መንገዶች ነው? በቃሉና በድርጅቱ አማካኝነት አመራር ይሰጠናል። (ኢሳ 48:17) ኃያል የሆነውን ቅዱስ መንፈሱን ይሰጠናል። (ሉቃስ 11:13) በተጨማሪም ወንድሞቻችንንና እህቶቻችንን በማነሳሳት ማበረታቻና ተግባራዊ እርዳታ እንዲሰጡን ያደርጋል። (2ቆሮ 7:6) ከዚህ አንጻር ይሖዋ የወንድሞቻችንን ሸክም ለማቅለል ማናችንንም ሊጠቀም ይችላል።
ለዘላለም የሚኖረውን ፍቅር በጉባኤ ውስጥ አሳዩ—ለአረጋውያን የተባለውን ቪዲዮ አጫውት። ከዚያም እንዲህ ብለህ ጠይቅ፦
የአንድን አረጋዊ ክርስቲያን ሸክም ለማቅለል ምን ማድረግ ትችላለህ?
ለዘላለም የሚኖረውን ፍቅር በጉባኤ ውስጥ አሳዩ—ለሙሉ ጊዜ አገልጋዮች የተባለውን ቪዲዮ አጫውት። ከዚያም እንዲህ ብለህ ጠይቅ፦
የአንድን የሙሉ ጊዜ አገልጋይ ሸክም ለማቅለል ምን ማድረግ ትችላለህ?
ለዘላለም የሚኖረውን ፍቅር በጉባኤ ውስጥ አሳዩ—ከሌላ አገር ለመጡ የተባለውን ቪዲዮ አጫውት። ከዚያም እንዲህ ብለህ ጠይቅ፦
አስቸጋሪ ሁኔታ ያጋጠማቸውን ክርስቲያኖች ሸክም ለማቅለል ምን ማድረግ ትችላለህ?
8. የጉባኤ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት
(30 ደቂቃ) bt ምዕ. 13 አን. 1-7፣ የክፍል 5 ማስተዋወቂያ እና በገጽ 103 ላይ ያለው ሣጥን