የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • mwb25 መጋቢት ገጽ 14-15
  • ከሚያዝያ 28–ግንቦት 4

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • ከሚያዝያ 28–ግንቦት 4
  • ክርስቲያናዊ ሕይወታችንና አገልግሎታችን​—የስብሰባው አስተዋጽኦ—2025
ክርስቲያናዊ ሕይወታችንና አገልግሎታችን​—የስብሰባው አስተዋጽኦ—2025
mwb25 መጋቢት ገጽ 14-15

ከሚያዝያ 28–ግንቦት 4

ምሳሌ 11

መዝሙር 90 እና ጸሎት | የመግቢያ ሐሳብ (1 ደቂቃ)

ከአምላክ ቃል የሚገኝ ውድ ሀብት

1. አትናገሩ!

(10 ደቂቃ)

‘በባልንጀራችሁ’ ላይ ጉዳት ሊያደርስ የሚችል ነገር አትናገሩ (ምሳሌ 11:9፤ w02 5/15 26 አን. 4)

ክፍፍል የሚፈጥር ነገር ከመናገር ተቆጠቡ (ምሳሌ 11:11፤ w02 5/15 27 አን. 2-3)

ሚስጥር አታውጡ (ምሳሌ 11:12, 13፤ w02 5/15 27 አን. 5)

ሁለት ወንድሞች ስብሰባ አዳራሽ ውስጥ እርስ በርስ ሲያወሩ። አንደኛው ወንድም ወደ እነሱ እየመጣ ስላለ ሌላ ወንድም አሉታዊ ነገር ይናገራል።

ለማሰላሰል የሚረዳ ጥያቄ፦ በሉቃስ 6:45 ላይ የሚገኘው ኢየሱስ የተናገረው ሐሳብ ጎጂ ንግግርን ለማስወገድ የሚረዳን እንዴት ነው?

2. መንፈሳዊ ዕንቁዎች

(10 ደቂቃ)

  • ምሳሌ 11:17—ደግነት ማሳየታችን የሚጠቅመን እንዴት ነው? (g20.1 11 ሣጥን)

  • ከዚህ ሳምንት የመጽሐፍ ቅዱስ ንባብ ምን መንፈሳዊ ዕንቁዎች አግኝታችኋል?

3. የመጽሐፍ ቅዱስ ንባብ

(4 ደቂቃ) ምሳሌ 11:1-20 (th ጥናት 5)

በአገልግሎት ውጤታማ ለመሆን ተጣጣር

4. ውይይት መጀመር

(4 ደቂቃ) መደበኛ ያልሆነ ምሥክርነት። በቅርቡ በስብሰባ ላይ ያገኘኸውን ትምህርት ለግለሰቡ ለመናገር አጋጣሚ ፈልግ። (lmd ምዕራፍ 2 ነጥብ 4)

5. ተመላልሶ መጠየቅ

(4 ደቂቃ) መደበኛ ያልሆነ ምሥክርነት። በማስተማሪያ መሣሪያዎቻችን ውስጥ የሚገኝ ቪዲዮ ተጠቀም። (lmd ምዕራፍ 8 ነጥብ 3)

6. ደቀ መዛሙርት ማድረግ

(4 ደቂቃ) የአደባባይ ምሥክርነት። የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት እንዲጀምር ጋብዝ፤ እንዲሁም ጥናቱ እንዴት እንደሚካሄድ አሳየው። (lmd ምዕራፍ 10 ነጥብ 3)

ክርስቲያናዊ ሕይወት

መዝሙር 157

7. አንደበታችሁ ሰላም እንዲያደፈርስ አትፍቀዱ

(15 ደቂቃ) ውይይት።

ፍጹማን ስላልሆንን በንግግራችን መሳሳታችን አይቀርም። (ያዕ 3:8) ሆኖም ንግግራችን ሊያስከትል የሚችለውን ጉዳት ማሰባችን በኋላ ላይ የምንጸጸትበትን ነገር ከመናገር እንድንቆጠብ ይረዳናል። የጉባኤውን ሰላም ሊያደፈርሱ ከሚችሉ አነጋገሮች መካከል የሚከተሉት ይገኙበታል፦

  • ጉራ። እንዲህ ያለው ለራስ የሚቀርብ ውዳሴ ፉክክርና ቅናት ሊቀሰቅስ ይችላል።—ምሳሌ 27:2

  • ሐቀኝነት የጎደለው አነጋገር። እንዲህ ያለው አነጋገር ዓይን ያወጣ ውሸትን ብቻ ሳይሆን አንድን ሰው ለማታለል ተብሎ የሚነገርን ንግግር ያካትታል። ሐቀኝነትን በትንሹም እንኳ ማጓደል ሌሎች እምነት እንዳይጥሉብን ሊያደርግና መልካም ስማችንን ሊያበላሽ ይችላል።—መክ 10:1

  • ጎጂ ሐሜት። ሐሜት የሚባለው ስለ ሰዎች የሚነገር እውነት ያልሆነ ወይም የግል ሚስጥራቸውን የሚያጋልጥ ወሬ ነው። (1ጢሞ 5:13) እንዲህ ያለው አነጋገር ወደ ጠብና ወደ ክፍፍል ሊመራ ይችላል

  • ቁጣ። በአንድ ሰው ላይ ስንበሳጭ የምንናገረው ከቁጥጥር ውጭ የሆነ ንግግር ነው። (ኤፌ 4:26) እንዲህ ያለው አነጋገር ሰዎችን ይጎዳል።—ምሳሌ 29:22

“ሰላም የሚያደፈርሱ ነገሮችን ‘አውልቃችሁ ጣሉ’​—ተቀንጭቦ የተወሰደ” ከተባለው ቪዲዮ የተወሰዱ ትዕይንቶች። 1. ኤሚሊ እና ሲልያ ካፌ ውስጥ ፊት ለፊት እየተያዩ ተቀምጠው። ሲልያ፣ ሄይሊ ማኅበራዊ ሚዲያዋ ላይ ፖስት ያደረገችውን ነገር ስልክ ላይ ስትመለከት። 2. በስብሰባ አዳራሹ የመኪና ማቆሚያ ቦታ ሄይሊ ሲልያን በቁጣ ስትናገራት።

ሰላም የሚያደፈርሱ ነገሮችን ‘አውልቃችሁ ጣሉ’—ተቀንጭቦ የተወሰደ የተባለውን ቪዲዮ አጫውት። ከዚያም እንዲህ ብለህ ጠይቅ፦

  • አነጋገራችን የጉባኤውን ሰላም በቀላሉ ሊያደፈርስ የሚችልበትን መንገድ በተመለከተ ምን ትምህርት አግኝታችኋል?

በጉባኤው ውስጥ መልሰው ሰላም ማስፈን የቻሉት እንዴት እንደሆነ ለማየት ‘ሰላምን ፈልጉ፤ ተከተሉትም’ የተባለውን ቪዲዮ ተመልከት።

8. የጉባኤ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት

(30 ደቂቃ) bt ምዕ. 25 አን. 14-21

የመደምደሚያ ሐሳብ (3 ደቂቃ) | የ2025 የክልል ስብሰባ አዲስ መዝሙር እና ጸሎት

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ