የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • mwb25 ግንቦት ገጽ 4-5
  • ከግንቦት 12-18

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • ከግንቦት 12-18
  • ክርስቲያናዊ ሕይወታችንና አገልግሎታችን​—የስብሰባው አስተዋጽኦ—2025
ክርስቲያናዊ ሕይወታችንና አገልግሎታችን​—የስብሰባው አስተዋጽኦ—2025
mwb25 ግንቦት ገጽ 4-5

ከግንቦት 12-18

ምሳሌ 13

መዝሙር 34 እና ጸሎት | የመግቢያ ሐሳብ (1 ደቂቃ)

ከአምላክ ቃል የሚገኝ ውድ ሀብት

1. “የክፉዎች መብራት” አያታላችሁ

(10 ደቂቃ)

ክፉዎች ምንም የወደፊት ተስፋ የላቸውም (ምሳሌ 13:9፤ w03 9/15 24 አን. 5-6)

መጥፎ ነገሮችን ጥሩ አስመስለው ከሚያቀርቡ ሰዎች ጋር አትወዳጁ (ምሳሌ 13:20፤ w12 7/15 12 አን. 3)

ይሖዋ ጻድቃንን ይባርካል (ምሳሌ 13:25፤ w04 7/15 31 አን. 6)

ሥዕሎች፦ የይሖዋ ምሥክር ያልሆነ አንድ ሰው የሚያደርጋቸውን መጥፎ ምርጫዎች አንዳንድ የይሖዋ ምሥክሮች ከሚያደርጓቸው ጥሩ ምርጫዎች ጋር የሚያወዳድሩ ሥዕሎች። 1. አንድ ሰው በእጁ መጠጥ ይዞ የምሽት ክለብ ውስጥ ሲደንስ። 2. በኋላ ላይ ታሞ መድኃኒት ሲወስድ። 3. አመሻሹ ላይ ሰብሰብ ብለው እየተጫወቱ ያሉ ወንድሞችና እህቶች ይዘምራሉ፣ ይደንሳሉ እንዲሁም አብረው ይመገባሉ። 4. በቀጣዩ ቀን በመስክ አገልግሎት ሲካፈሉ።

ዓለማዊ ምኞቶችን የሚያሳድዱ ሰዎች ሕይወት ከውጭ እንደሚታየው አጓጊ አይደለም። የይሖዋን ፈቃድ የሚያደርጉ ሰዎች ግን በሕይወታቸው እውነተኛ እርካታ ያገኛሉ

2. መንፈሳዊ ዕንቁዎች

(10 ደቂቃ)

  • ምሳሌ 13:24—ይህ ጥቅስ ስለ ፍቅርና ስለ ተግሣጽ ምን ያስተምረናል? (w08 4/1 14 አን. 3-5)

  • ከዚህ ሳምንት የመጽሐፍ ቅዱስ ንባብ ምን መንፈሳዊ ዕንቁዎች አግኝታችኋል?

3. የመጽሐፍ ቅዱስ ንባብ

(4 ደቂቃ) ምሳሌ 13:1-17 (th ጥናት 10)

በአገልግሎት ውጤታማ ለመሆን ተጣጣር

4. ውይይት መጀመር

(3 ደቂቃ) ከቤት ወደ ቤት። ወቅታዊ ርዕሰ ጉዳይ በማንሳት ከጀመርክ በኋላ የግለሰቡን ትኩረት ይበልጥ ስለሚስበው ሌላ ርዕሰ ጉዳይ የመጽሐፍ ቅዱስ ሐሳብ አካፍል። (lmd ምዕራፍ 2 ነጥብ 5)

5. ውይይት መጀመር

(4 ደቂቃ) መደበኛ ያልሆነ ምሥክርነት። ግለሰቡ በስብሰባችን ላይ እንዲገኝ ጋብዝ። (lmd ምዕራፍ 2 ነጥብ 3)

6. ንግግር

(5 ደቂቃ) lmd ተጨማሪ መረጃ ሀ ነጥብ 9—ጭብጥ፦ ወላጆቻቸውን የሚያከብሩና የሚታዘዙ ልጆች ይሳካላቸዋል። (th ጥናት 16)

ክርስቲያናዊ ሕይወት

መዝሙር 77

7. “የጻድቃን ብርሃን ደምቆ ይበራል”

(8 ደቂቃ) ውይይት።

የአምላክ ቃል ወደር የለሽ እውቀትና ጥበብ ይዟል። በቃሉ ውስጥ በሚገኘው ብርሃን ሕይወታችንን ከመራን ዘላቂ ስኬትና ደስታ እናገኛለን። ዓለም እንዲህ ያለ ነገር ሊሰጠን አይችልም።

“ዓለም የሌለውን ነገር ሊሰጣችሁ አይችልም” ከተባለው ቪዲዮ የተወሰደ ሥዕል። እህት ጋይናንሽና ሜዳ ላይ ቁጭ ብላ ወደ ሰማይ ስትመለከት።

ዓለም የሌለውን ነገር ሊሰጣችሁ አይችልም የተባለውን ቪዲዮ አጫውት። ከዚያም እንዲህ ብለህ ጠይቅ፦

  • የእህት ጋይናንሽና ተሞክሮ “የጻድቃን ብርሃን” ‘ከክፉዎች መብራት’ ያለውን ብልጫ የሚያሳየው እንዴት ነው?—ምሳሌ 13:9

በዚህ ዓለም ውስጥ ያሉትን ነገሮች ለማግኘት በመጎምጀት ወይም ይሖዋን ለማገልገል ስትሉ በከፈላችኋቸው መሥዋዕቶች በመቆጨት ጊዜ አታባክኑ። (1ዮሐ 2:15-17) ከዚህ ይልቅ ያገኛችሁት እውቀት ባለው “የላቀ ዋጋ” ላይ አተኩሩ።—ፊልጵ 3:8

ለቤተሰብ አምልኮ የሚሆን ሐሳብ፦

እውነት ሕይወትን ይለውጣል በሚለው ዓምድ ውስጥ ያሉ አንድ ወይም ሁለት ቪዲዮዎችን አልፎ አልፎ ተመልከቱ። ቪዲዮው እውነት ያለውን ዋጋ የሚያሳየው እንዴት እንደሆነ ተወያዩ።

8. ለጉባኤው እንደሚያስፈልግ

(7 ደቂቃ)

9. የጉባኤ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት

(30 ደቂቃ) bt ምዕ. 26 አን. 9-17

የመደምደሚያ ሐሳብ (3 ደቂቃ) | መዝሙር 43 እና ጸሎት

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ