የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • w24 መጋቢት ገጽ 32
  • “በቀደሙት ዘመናት የተፈጸሙትን ኃጢአቶች ይቅር ብሏል”

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • “በቀደሙት ዘመናት የተፈጸሙትን ኃጢአቶች ይቅር ብሏል”
  • የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2024
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • ቤዛው—ከሁሉ የላቀ የአምላክ ስጦታ
    ትክክለኛው የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ምንድን ነው?
  • ቤዛው—ከሁሉ የላቀ የአምላክ ስጦታ
    መጽሐፍ ቅዱስ ምን ያስተምረናል?
  • ለቤዛው አድናቆት ማሳየታችሁን ቀጥሉ
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2021
  • ቤዛው አምላክ ጻድቅ መሆኑን ያጎላል
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2005
ለተጨማሪ መረጃ
የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2024
w24 መጋቢት ገጽ 32

የመጽሐፍ ቅዱስ አገላለጽ

“በቀደሙት ዘመናት የተፈጸሙትን ኃጢአቶች ይቅር ብሏል”

ለኃጢአታችን ይቅርታ ማግኘት የምንችለው ኢየሱስ በደሙ በከፈለው ቤዛዊ መሥዋዕት አማካኝነት ብቻ ነው። (ኤፌ. 1:7) ይሁንና መጽሐፍ ቅዱስ “አምላክ ቻይ በመሆን በቀደሙት ዘመናት [ማለትም ኢየሱስ ቤዛውን ከመክፈሉ በፊት] የተፈጸሙትን ኃጢአቶች ይቅር ብሏል” ይላል። (ሮም 3:25) ይሖዋ ፍጹም የሆነውን የፍትሕ መሥፈርቱን ሳይጥስ ይህን ማድረግ የቻለው እንዴት ነው?

ይሖዋ እምነት ያላቸውን የሰው ልጆች የሚያድን “ዘር” እንደሚያዘጋጅ ከወሰነበት ቅጽበት አንስቶ በእሱ ዓይን ቤዛው እንደተከፈለ ሊቆጠር ይችላል። (ዘፍ. 3:15፤ 22:18) አምላክ፣ ጊዜው ሲደርስ አንድያ ልጁ ቤዛውን በፈቃደኝነት እንደሚከፍል ሙሉ በሙሉ እርግጠኛ ነበር። (ገላ. 4:4፤ ዕብ. 10:7-10) ኢየሱስ የአምላክ ወኪል ሆኖ በምድር ላይ በኖረበት ወቅት ገና ቤዛው ባይከፈልም እንኳ የሰዎችን ኃጢአት ይቅር የማለት ሥልጣን ነበረው። ይህን ያደረገው፣ ወደፊት የሚከፈለው ቤዛ እምነት ያላቸውን ሰዎች ኃጢአት እንደሚሸፍን ስላወቀ ነው።—ማቴ. 9:2-6

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ