መዝሙር 123
እረኞች—ስጦታ የሆኑ ወንዶች
በወረቀት የሚታተመው
(ኤፌሶን 4:8)
1. መንጋውን ’ሚጠብቁ ወንዶች፣
አምላካችን ሰጠን፤
መንገድ የሚመሩን እረኞች፣
ምሳሌ በመሆን።
(አዝማች)
አምላክ ሰጥቶናል ታማኝ ወንዶች፣
እውነተኛ እረኞች።
ለመንጋው ’ሚጨነቁ ናቸው፤
ምንጊዜም አድንቋቸው።
2. በርኅራኄ ይይዙናል፣
በፍቅር በመምራት።
ከአምላክ መንገድ እንዳንወጣ፣
ምክር ይሰጡናል።
(አዝማች)
አምላክ ሰጥቶናል ታማኝ ወንዶች፣
እውነተኛ እረኞች።
ለመንጋው ’ሚጨነቁ ናቸው፤
ምንጊዜም አድንቋቸው።
3. ስንጎዳ ይጠግኑናል፣
በቃል በማጽናናት።
ሁሌ እንድናገለግለው፣
ያበረታቱናል።
(አዝማች)
አምላክ ሰጥቶናል ታማኝ ወንዶች፣
እውነተኛ እረኞች።
ለመንጋው ’ሚጨነቁ ናቸው፤
ምንጊዜም አድንቋቸው።
(በተጨማሪም ኢሳ. 32:1, 2ን፣ ኤር. 3:15ን፣ ዮሐ. 21:15-17ን እና ሥራ 20:28ን ተመልከት።)