የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • lfb ትምህርት 5 ገጽ 18-ገጽ 19 አን. 5
  • የኖኅ መርከብ

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • የኖኅ መርከብ
  • ከመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች ምን ትማራለህ?
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • ኖኅ መርከብ ሠራ
    የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች መማሪያ መጽሐፌ
  • ታላቁ የጥፋት ውኃ—አምላክን የሰሙት እነማን ነበሩ? ያልሰሙትስ?
    አምላክን ስማ የዘላለም ሕይወት ታገኛለህ
  • “ከእውነተኛው አምላክ ጋር ይሄድ ነበር”
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2013
  • “ከእውነተኛው አምላክ ጋር ይሄድ ነበር”
    በእምነታቸው ምሰሏቸው
ለተጨማሪ መረጃ
ከመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች ምን ትማራለህ?
lfb ትምህርት 5 ገጽ 18-ገጽ 19 አን. 5
ኖኅና ቤተሰቡ መርከቡን ሲሠሩ

ትምህርት 5

የኖኅ መርከብ

ከጊዜ በኋላ በምድር ላይ የሚኖሩት ሰዎች ቁጥር እየጨመረ መጣ። አብዛኞቹ ሰዎች ክፉዎች ነበሩ። በሰማይ ይኖሩ የነበሩ አንዳንድ መላእክትም እንኳ ክፉዎች ሆኑ። በሰማይ ያለውን መኖሪያቸውን ትተው ወደ ምድር ወረዱ። ለምን እንዲህ እንዳደረጉ ታውቃለህ? እንደ ሰው ሆነው ሴቶችን ማግባት ስለፈለጉ ነው።

መላእክቱና ሴቶቹ ተጋብተው ልጆች ወለዱ። እነዚህ ልጆች ሲያድጉ በጣም ጠንካራና ጉልበተኛ ሆኑ። ሰዎችንም መጉዳት ጀመሩ። ይሖዋ ይህ ሁኔታ እንዲቀጥል አልፈለገም። ስለሆነም ክፉ ሰዎችን በውኃ ለማጥፋት ወሰነ።

ኖኅና ቤተሰቡ መርከቡን ሲሠሩና ምግብ ሲያዘጋጁ

ሆኖም ከእነዚህ ሰዎች የተለየ አንድ ሰው ነበር። ይህ ሰው ኖኅ ይባላል፤ እሱም ይሖዋን በጣም ይወድ ነበር። ኖኅ ሚስትና ሦስት ወንዶች ልጆች ነበሩት፤ የልጆቹ ስም ሴም፣ ካምና ያፌት ሲሆን ሁሉም ሚስት ነበራቸው። ይሖዋ ኖኅን፣ እሱና ቤተሰቡ ከጥፋት ውኃው መትረፍ እንዲችሉ ትልቅ መርከብ እንዲሠራ ነገረው። ኖኅ የሠራው መርከብ በውኃ ላይ መንሳፈፍ የሚችል ትልቅ ሣጥን ይመስል ነበር። ይሖዋ ኖኅን እንስሳትም መትረፍ እንዲችሉ ወደ መርከቡ እንዲያስገባቸው ነገረው።

ኖኅ ወዲያውኑ መርከቡን መሥራት ጀመረ። ኖኅና ቤተሰቡ መርከቡን ሠርተው ለመጨረስ 50 ዓመት አካባቢ ፈጅቶባቸዋል። መርከቡን ልክ ይሖዋ እንዳዘዛቸው አድርገው ሠሩ። ኖኅ መርከቡን እየሠራ በነበረበት ጊዜ ሰዎች ከጥፋት ውኃው እንዲድኑ ያስጠነቅቅ ነበር። ግን ማንም አልሰማውም።

በመጨረሻም ወደ መርከቡ የሚገቡበት ጊዜ ደረሰ። እስቲ ቀጥሎ ምን እንደሆነ እንመልከት።

“በኖኅ ዘመን እንደነበረው ሁሉ የሰው ልጅ መገኘትም እንደዚሁ ይሆናል።”—ማቴዎስ 24:37

ጥያቄ፦ ይሖዋ የጥፋት ውኃ ለማምጣት የወሰነው ለምንድን ነው? ይሖዋ ለኖኅ ምን መመሪያ ሰጠው?

ዘፍጥረት 6:1-22፤ ማቴዎስ 24:37-41፤ 2 ጴጥሮስ 2:5፤ ይሁዳ 6

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ