መግቢያ
ምን ይመስልሃል?
በራእይ መጽሐፍ ውስጥ የሚገኘውን ስለ አራቱ ፈረሰኞች የሚናገረውን ትንቢት ብዙዎች ያውቁታል። ይህ ትንቢት አንዳንዶችን ያስፈራቸዋል። ሌሎች ደግሞ ስለዚህ ትንቢት ይበልጥ ለማወቅ ይጓጓሉ። መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ስላሉ ትንቢቶች ምን እንደሚል ተመልከት፦
“የዚህን ትንቢት ቃል ጮክ ብሎ የሚያነብ ደስተኛ ነው፤ እንዲሁም ቃሉን የሚሰሙትና በውስጡ የተጻፉትን ነገሮች የሚጠብቁት ደስተኞች ናቸው።”—ራእይ 1:3
ይህ የመጠበቂያ ግንብ እትም የአራቱ ፈረሰኞች ግልቢያ ለእኛ ምሥራች ሊሆን የሚችለው እንዴት እንደሆነ ያብራራል።