የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • km 11/94 ገጽ 2
  • ምን ዓይነት መንፈስ ታሳያላችሁ?

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • ምን ዓይነት መንፈስ ታሳያላችሁ?
  • የመንግሥት አገልግሎታችን—1994
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • በጉባኤያችሁ ውስጥ ጥሩ መንፈስ እንዲሰፍን አድርጉ
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2012
  • የምታሳዩት መንፈስ ምን ዓይነት ነው?
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2012
  • “በመንፈስ የጋላችሁ ሁኑ”
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2009
  • ስለ አምላክ ጸጋ የሚገልጸውን ምሥራች አውጁ
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2016
ለተጨማሪ መረጃ
የመንግሥት አገልግሎታችን—1994
km 11/94 ገጽ 2

ምን ዓይነት መንፈስ ታሳያላችሁ?

1 ጳውሎስ በፊልጵስዩስ ለሚገኘው ጉባኤ የጻፈውን ደብዳቤ በዚህ ጥብቅ ማሳሰቢያ ደመደመ:- “ይገባናል የማንለው የጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ደግነት ከምታሳዩት መንፈስ ጋር ይሁን።” (ፊልጵ. 4:23 አዓት) ምሥራቹን ለመስበክ ስለነበራቸው ልባዊ ፍላጎትም ሆነ አንዱ ለሌላው ደኅንነት ላሳየው ሞቅ ያለ ፍቅራዊ አሳቢነት አመሰገናቸው።— ፊልጵ. 1:3–5፤ 4:15, 16

2 በጉባኤያችንም ተመሳሳይ መንፈስ ለማንጸባረቅ መፈለግ አለብን። ሁሉም ቅንዓትን፣ ደግነትንና እንግዳ ተቀባይነትን ሲያሳዩ ተመልካቾች ይህን ሁኔታ በግልጽ ይመለከታሉ። አዎንታዊና ፍቅራዊ የሆነ መንፈስ አንድነትና መንፈሳዊ እድገት ያስገኛል። (1 ቆሮ. 1:10) አሉታዊ መንፈስ ግን ተስፋ መቁረጥንና በግማሽ ልብ መሥራትን ያስከትላል። — ራእይ 3:15, 16

3 ሽማግሌዎች ቀዳሚ ይሆናሉ፦ ሽማግሌዎች በመካከላቸውና በጉባኤው ውስጥ ጥሩ የሆነ አዎንታዊ መንፈስ እንዲኖር የማድረግ ኃላፊነት አላቸው። ለምን? ምክንያቱም ጉባኤው እነርሱ በሚያሳዩት መንፈስና ጠባይ ሊነካ ስለሚችል ነው። በመስክ አገልግሎት ቀናተኛ የሆኑ፣ ሞቅ ባለ ፈገግታና ደግነት በታከለበት ቃል ሰላም የሚሉን እንዲሁም በግልም ሆነ ከመድረክ አዎንታዊና የሚገነባ ምክር በሚሰጡ ሽማግሌዎች ደስ ይለናል። — ዕብ. 13:7

4 እርግጥ ጉባኤው የወዳጅነት መንፈስ የሚያንጸባርቅ፣ እንግዳ ተቀባይ፣ ቀናተኛና መንፈሳዊ አስተሳሰብ ያለው እንዲሆን ሁላችንም የበኩላችንን አስተዋጽዖ ማድረግ አለብን። በግላችን ከሌሎች ጋር በመቀራረብ ሞቅ ያለ ስሜትና ፍቅር ልናሳይ እንችላለን። (1 ቆሮ. 16:14) በመካከላችን በዕድሜ፣ በዘር፣ በትምህርት ደረጃ ወይም በሀብት ልዩነት የመፍጠር አዝማሚያ መኖር የለበትም። (ከኤፌሶን 2:21 ጋር አወዳድር።) ባለን ተስፋ ምክንያት የደስታ፣ በልግስና እንግዳ የመቀበልና በአገልግሎት ቀናተኛ የመሆን መንፈስ ልናሳይ እንችላለን። — ሮሜ 12:13፤ ቆላ. 3:22, 23

5 አዲሶችን ጨምሮ ከእኛ ጋር የሚሰበሰቡ ሁሉ ጥሩ መስተንግዶ እንደተደረገላቸው እንዲረዱና የወንድማማችነትን ፍቅርና አድናቆት እንዲሰማቸው ሊደረግ ይገባል። በአገልግሎታችንና ጥሩ መንፈሳዊ ባሕርያትን በማንጸባረቅ ጉባኤው “የእውነት አምድና ድጋፍ” መሆኑን እናረጋግጣለን። (1 ጢሞ. 3:15 አዓት) በተጨማሪም ልባችንንና የማሰብ ኃይላችንን በሚጠብቅ “የእግዚአብሔር ሰላም” አማካኝነት መንፈሳዊ መረጋጋት እናገኛለን። (ፊልጵ. 4:6, 7) በጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ አማካይነት ይገባናል የማንለውን የይሖዋን ደግነት የሚያተርፍልን መንፈስ ለማሳየት ሁላችንም በትጋት እንጣር። — 2 ጢሞ. 4:22 አዓት

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ